የአገልግሎት መ/ቤታችን እ.ኤ.እ በ2026 በጀት ዓመት ለሥራ አገልግሎት የሚዉል የMicrosoft 365 E1 የተጠቃሚ ቁጥር 400፣ Microsoft 365 E3 የተጠቃሚ ቁጥር 100 የአገልግሎት ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
የMicrosoft 365 E1 የተጠቃሚ ቁጥር 400፣ Microsoft 365 E3 የተጠቃሚ ቁጥር 100 ግዥ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር፡- ስተአ/002/2026
የአገልግሎት መ/ቤታችን እ.ኤ.እ በ2026 በጀት ዓመት ለሥራ አገልግሎት የሚዉል የMicrosoft 365 E1 የተጠቃሚ ቁጥር 400፣ Microsoft 365 E3 የተጠቃሚ ቁጥር 100 የአገልግሎት ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የሚፈለግባቸውን ማንኛውንም የመንግሥት ግብር አጠናቅቀው ለመክፈላቸው ከግብር ሰብሳቢ መሥሪያ ቤት የተሰጠ ማስረጃ፣ የታደሰ የንግድ ሥራ ፍቃድ እና የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣ በጨረታ ለመሳተፍ በኢፌዴሪ መንግሥት ግዥ እና ንብረት ባለሥልጣን በአቅራቢነት የተመዘገቡ እንዲሁም የተ.እ.ታ. ምዝገባ ሠርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ ድርጅቶችን፣ በብሔራዊ ግልፅ የጨረታ ዘዴ አወዳድሮ ውል በመግባት የሚፈፀም ይሆናል፡፡
በመሆኑም ተጫራቾች፡-
1) የጨረታ ሰነዱን አዲስ አበባ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ከሚገኘው የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ዋና መ/ቤት የፋይናንስ ቡድን ቢሮ በመምጣትና የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ) በመክፈል ለ10 ተከታታይ ሥራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት እስከ 6፡30 ሰዓት ፣ ከሰዓት ከ7፡30 እስከ 11፡30 ባለው ጊዜ ውስጥ መግዛት ይቻላሉ፡፡ ቅዳሜና እሑድ የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ሥራ ቀናት አይደሉም፡፡
2) ማንኛውም ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ጥቅል ዋጋ 2 /ሁለት/ በመቶ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በ F.D.R.E Refugees and Returnees Service ሥም በተዘጋጀ የባንክ የክፍያ ማዘዣ (CPO) ወይም በቅድመ-ሁኔታ ያልተገደበ የባንክ ዋስትና ደብዳቤ፣ የአገልግሎቱን ዋጋ፣ በቀረበው ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ መሠረት የቴክኒክ ሰነድ እና እንዲሁም በጨረታ ሰነዱ የተዘረዘሩትን የብቃትና የልምድ ማስረጃዎች ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል። የሚያያዙ ማስረጃዎች በሙሉ የአገልግሎት ጊዜያቸው ያላበቃላቸው መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
3) የመጫረቻ ሰነዳቸውን ቴክኒካል እና ፋይናንሺያል ሰነድ አንድ ኦርጅናል እና አንድ ኮፒ ለየብቻው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር እስከ 10ኛው የስራ ቀን 8፡00 ሰዓት ድረስ ከታች በተመለከተው አድራሻ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት የሚችሉ ሲሆን ጨረታው በዚሁ ዕለት ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአገልግሎት መስሪያ ቤቱ የሰራተኞች ክበብ ይከፈታል። ሆኖም ይህ ቀን ቅዳሜና እሑድ ወይም በበዓላት ቀን ከዋለ፣ የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተጠቀሰው ቦታና ሰዓት ይሆናል።
4) መሥሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት
የእንቁላል ፋብሪካ አደባባይን ሳደሻገሩ
ከፌዴራል ፖሊስ ክበብ ፊት ለፊት
ስልክ ቁጥር 09-97-23-66-31
በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት
