የፋና ቦሌ ሸ/ኃ/የተ/ሕ/ስራ ማህበር ከ22 ማዞሪያ ወደ አዲሱ እስታዲየም በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘው 17/18 ማዕከል 1,400 ካሬ ላይ ያረፈ ጂ+4-ቴራስ እያሰራው ባለው ሞል ላይ የሚገኙትን የንግድ ቦታዎች ለባንኮች ለምግብ ቤቶች፣ ለካፌና ሬስቶራንቶች፣ ለልብስና ጫማ መሸጫ፣ ለቢሮዎችና ለተለያዩ ንግድ አገልግሎት የሚሆን ሱቆች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የፋና ቦሌ ሸ/ኃ/የተ/ሕ/ስራ ማህበር ከ22 ማዞሪያ ወደ አዲሱ እስታዲየም በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘው 17/18 ማዕከል 1,400 ካሬ ላይ ያረፈ ጂ+4-ቴራስ እያሰራው ባለው ሞል ላይ የሚገኙትን የንግድ ቦታዎች ለባንኮች ለምግብ ቤቶች፣ ለካፌና ሬስቶራንቶች፣ ለልብስና ጫማ መሸጫ፣ ለቢሮዎችና ለተለያዩ ንግድ አገልግሎት የሚሆን ሱቆች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ቦታው ለስራ አመቺ የሆነ እና አስፋልት ዳር እንዲሁም የጄኔሬተር እና የከርሰ ምድር ውሃ የተሟላ መሆኑን እና ኪራዩ የሚጀምረው ከ3 እስከ 4 ወር ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ መሆኑን አውቀው መጫረት የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
1. የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ CPO ከሚያቀርቡት ዋጋ 2% ማቅረብ አለባቸው።
2. ተጫራቾች የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ/ በመክፈል የጨረታውን ሰነድ ከሻላ መናፈሻ ፋይናንስ ክፍል ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡
3. ከላይ የተዘረዘሩ መረጃዎችና ሰነዶች አሟልተው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ አስራ አምስት ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ እስከ 11፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
4. ጨረታው በአስራ ስድስተኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልጽ ሻላ 17/17 ህብረተሰብ ልማት ማዕከል ይከፈታል፡፡ በዕለቱ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ያለመገኘት የጨረታ ሣጥን መክፈቻ ሥነ-ሥርዓትን አያስተጓጉልም፡፡
5. አሻሚ፣ የተሰረዘ፣ የተደለዘ እና ግልፅ ባልሆነ ሁኔታ የጨረታ ዋጋ በመሙላት መወዳደር ከጨረታ ውጭ ያደርጋል።
6. የጨረታውን መመሪያ አለማክበር ከጨረታው ያሰርዛል፤
7. ፋና ቦሌ ሸማቾች ኃላ/የተ/የህ/ሥ/ማህበር ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ ማብራሪያ ስልክ ቁጥር +251 9 65 44 88 88/09 56 44 88 88 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
የፋና ቦሌ ሸ/ኃ/የተ/ሕ/ስራ ማህበር
