የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ቁሳቁስ የማሸግ፣ የእሸጋ ጥራት የማረጋገጥ እና በአይሮፕላን የመጡ ዕቃዎችን በትኖ መኪና ላይ የመጫን አገልግሎት ግዥ በብሄራዊ ግልጽ ጨረታ በሎት አወዳድሮ አገልግሎቱን መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡ NEBE/NCB/13/2018
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ቁሳቁስ የማሸግ፣ የእሸጋ ጥራት የማረጋገጥ እና በአይሮፕላን የመጡ ዕቃዎችን በትኖ መኪና ላይ የመጫን አገልግሎት ግዥ በብሄራዊ ግልጽ ጨረታ በሎት አወዳድሮ አገልግሎቱን መግዛት ይፈልጋል፡፡
· ሎት 1- የምርጫ ሰነድና ቁሳቁስ እሸጋና ቦርዱ ባዘጋጀው ተሸከርካሪ የመጫን አገልግሎት ግዥ
· ሎት 2- የእሸጋ ሒደት ጥራት የማረጋገጥ አገልግሎት ግዥ
· ሎት 3- በአይሮፕላን የመጡ ዕቃዎችን በትኖ መኪና ላይ የመጫን አገልግሎት የሚሰጥ ማህበር /ድርጅት/ የአገልግሎት ግዥ
በዚሁ መሰረት፡
1- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የጨረታው ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መክፈቻ ቀን ድረስ የማይመለስ 200.00 /ሁለት መቶ/ ተጫራቾች በዘርፉ ያላቸውን በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት የግብር ክሊራንስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፤ በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ድረገጽ የተመዘገቡ ስለመሆናቸው ብር/ በመክፈል ከቦርዱ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 107 የጨረታውን ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡
2- ማስረጃቸውን እንዲሁም የተፈረመና ማህተም ያለው የማጭበርበር ድርጊት ላለመፈፀም ቃል የተገባበት ቅጽ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
3- ተጫራቾች ዋጋቸውን በመሙላት ቦርዱ ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ከጨረታ መዝጊያ ሰዓት በፊት ማስገባት አለባቸው፡፡ ጨረታው ከተዘጋ በኋላ የሚቀርቡና ስርዝ ድልዝ ያለው የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
4- ተጫራቾች ለጨረታው ማስከበርያነት ለሎት አንድ ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር)፣ ለሎት ሁለት 30,000.00 (ሰላሳ ሺ ብር) እና ለሎት ሶስት 30,000.00 (ሰላሳ ሺህ ብር) ያለ ቅድመ ሁኔታ በባንክ በተረጋገጠ ዋስትና ወይም ሲፒኦ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
5- ጨረታው መጋቢት 28 ቀን 2018 ከሰዓት በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከቀኑ በ8፡30 ላይ ተጫራቾችና ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቦርዱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
6- ቦርዱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
7- ተጨማሪ ማብራርያ ካስፈለገ በአካል ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አድራሻ ቦሌ መንገድ ፍላሚጎ ገባ ብሎ ባለው ዋ/መ/ቤት በመቅረብ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
አድራሻችን፡- ቦሌ ፍላሚንጎ ካፌ ገባ ብሎ
ስልክ ቁ:- +251 115153468
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ
