በጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በ2018 ዓ/ም በጀት ዓመት ለሥራ አገለግሎት የሚውል በዘርፉ ከተሰማሩ ሕጋዊ ከሆኑ አቅራቢዎች ከታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች ሆነ አገልግሎቶችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በ2018 ዓ/ም በጀት ዓመት ለሥራ አገለግሎት የሚውል በዘርፉ ከተሰማሩ ሕጋዊ ከሆኑ አቅራቢዎች ከታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች ሆነ አገልግሎቶችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም፡-
1ኛ የተለያዩ የፅዳት ዕቃ
2ኛ የተለያዩ የፅህፈት መሳሪያ
3ኛ ጎሚስታ
4ኛ የመፀዳጃ ቤት ፈሳሽ ማስወገጃ የመኪና ኪራይ
5ኛ ፍራሽ እና ትራስ
6ኛ የሚጫራቱበትን የዕቃ ዝርዝር የሚገልፅ ሰነድ የማይመለስ 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 ተከታታይ በሥራ ቀን በጉ/ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ፋይናንስ ግዥ አስተዳዳር ክፍል ቢሮ ቁጥር 7 ዘወትር በሥራ ሰዓት በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ።
7ኛ የሚጫራቱበትን የዕቃ ዋጋ የሚገልፅ ሰነድ በታሸገ ኤንቨሎፕ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ እስከ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን አስገብቶ ይታሸጋል።
8ኛ ተጫራቾች በተሰማሩበት የሥራ መስክ የዘመኑ ግብር ለመክፈላቸው ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው።
9ኛ ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ዕቃዎች ናሙና ከጨረታ መክፈቻ ቀናት አስቀድመው ማቅረብ ለሚችሉባቸው ዕቃዎች አንድአንድ ናሙና ማቅረብ አለባቸው
10ኛ ተጫራቾች በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ወይም ከአ/አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት የቢሮ ዕቃ አቅራቢዎች ዝርዝር ገፅ የተመዘገቡ ለመሆናቸው የምስክር ወረቀት አያይዘው ማቅረብ አለባችው።
11ኛ ተጫራቾች ከሚያቀረቡት ዋጋ በእያንዳንዱ ሎት ማለትም ተራ ቁጥር 1 እስከ………ድረስ ያሉትን ዕቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ 3,000.00 /ሶስት ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ CPO ብቻ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማስያዝ ይኖባቸዋል።
12ኛ አሸናፊው አሸናፊነቱ እንደተገለፀለት ወዲያው ለአሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ 10% የመልካም ሥራ አፈፃፀም ዋስትና በ CPO ብቻ ማስያዝ ይኖርበታል።
13ኛ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይህ ማስታወቂያ በተጠናቀቀበት 10ኛው የሥራ ቀን በመ/ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ በዛው ዕለት በቀኑ 11፡00 ሰዓት ታሽጎ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ተጫራቾቹ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው ይከፈታል። ቀኑ በሥራ ቀን ካልዋለ በሚቀጥለው በሥራ ቀን 3፡30 ሰዓት ጨረታው ይከፈታል።
14ኛ አማራጭ ዋጋ በዚህ ጨረታ ማቅረብ ወይም መጠቀም አይቻልም።
15ኛ መስሪያ ቤቱ በግዥ ወቅት 25% መጨመር መቀነስ ይችላል።
16ኛ መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 011 156 6407/ 09 44 07 63 24/ 09 20 29 88 66
ጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ
