የኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ህይወት አ/ማ ባስገነባው ሁለት የገበያ ማዕከል ህንፃዎች ላይ ያለን ነጋዴዎች በሱቆች መግቢያ በር ላይ ያሉ የአሉሚኒየም ፍሬሞችን ከነመስታወታቸው አስነቅሎ መሸጥ ይፈልጋል።
በድጋሚ የወጣ የአሉሚኒየም ፍሬምና መስታወት
ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
የኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ህይወት አ/ማ ባስገነባው ሁለት የገበያ ማዕከል ህንፃዎች ላይ ያለን ነጋዴዎች በሱቆች መግቢያ በር ላይ ያሉ የአሉሚኒየም ፍሬሞችን ከነመስታወታቸው አስነቅሎ መሸጥ ይፈልጋል።
1. ህንፃ 1 3ኛ ፎቅ ከሱቅ ቁጥር 1073 እስከ 1200 የሱቁ ብዛት 137
2. ህንፃ 2 3ኛ ፎቅ ከሱቅ ቁጥር 1319 እስከ 1492 የሱቅ ብዛት 204
ስለሆነም ከላይ የተጠቀሱትን ዕቃዎች የሚፈለጉ ተጫራቾች ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ከአ/ማህበሩ ህንፃ ብሎክ 2 ቢሮ ቁጥር 4 ላይ ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ወሰደው የሚገዙበትን ዋጋ እና የብር 100,000.00 CPO ብቻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎኘ ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ከታች በተጠቀሰው አድራሻ ማስገባት ይችላሉ። ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአክሲዮን ማህበሩ ጽ/ቤት ይከፈታል።
ኮሚቴው የተሻለ አማራጭ ካገኘ በጨረታው በከፊልም ሆነ ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማስታወሻ
· አድራሻ ኮልፌ አጠና ተራ ከቴሌው ጀርባ የኮልፌ ቅዱስ ራጉዔል አዲስ ሕይወት አ/ማህበር ብሎክ 2 አራተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 4፤
· የጨረታውን ሰነድ መውሰድ የሚቻለው ከጠዋት 2፡30 እስከ 6፡30 ከሰዓት 7፡30 እስከ10፡30 ብቻ ይሆናል፤
· ስልክ 09-32-08-03-77 ወይም 09-12-05-47-92
የኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ህይወት አ/ማ
