ዋንዛ ፈርኒሺንግ ኢንዱስትሪ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር ከታች የተዘረዘሩትን ለእንጨት ስራ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ጣውላዎችን በግልፅ ጨረታ ግዥ ዘዴ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ዋ/ፈ/ኢ/ጣግጨ /19/2018
ዋንዛ ፈርኒሺንግ ኢንዱስትሪ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር ከታች የተዘረዘሩትን ለእንጨት ስራ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ጣውላዎችን በግልፅ ጨረታ ግዥ ዘዴ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
|
ተ.ቁ |
የባህር ዛፍ ምሰሶ ቁመት |
ዝርዝር መግለጫ/Specification |
|
1 |
Local Pine (የፈረንጅ ጥድ፤ ሻሸመኔ) |
ቁመት፡ 4፡00 ሜትር |
|
2 |
Australi Solid Wood |
ቁመት፡ 4.00 ሜትር |
በመሆኑም ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሱ አቅራቢዎች በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋብዛል፤
· ተጫራቾች በዘርፉ መወዳደር የሚያስችል የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TN no) እና ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
· ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር) ከጨረታ መወዳደሪያ ኦሪጂናል ሰነድ ጋር በባንክ በተረጋገጠ ቼክ (CPO) ዋንዛ ፈርኒሺንግ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ወይም Wanza Furnishing industry Private Limited Company ስም ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፤
· ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዱን ሰሚት ፔፕሲ ፋብሪካ በስተጀርባ በሚገኘው በድርጅቱ አንደኛ ፎቅ የግዥ መምሪያ ክፍል ውስጥ በመቅረብ የማይመለስ 100 (አንድ መቶ) ብር በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፤ ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የሎካ ፓይነስ እና አውስትራሊያ - አይነት በግልፅ ለይተው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
· ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ እስከ ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከታች በተገለፀው አድራሻ ጠዋት 4፡00 ድረስ ማስገባት ይጠቅባቸዋል።
· ጨረታ ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 4፡30 ከታች በተገለጸው አድራሻና ቦታ ይከፈታል፤ ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የጨረታ ሰነዱ የሚገኝበት አድራሻ፡- ዋናው መ/ቤት አዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክ/ከ ወረዳ 10 የቤት ቁጥር አዲስ ሰሚት ከፔፕሲ ፋብሪካ በስተጀርባ በሚገኘው የዋንዛ ፈርኒሺንግ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር አንደኛ ፎቅ ግዥ መምሪያ ቢሮ።
ስልክ ቁጥር 0911-926283
ዋንዛ ፈርኒሺንግ ኢንዱስትሪ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር
