የጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ሎት 1 የቆርቆሮ አጥር ግንባታ የእጅ ዋጋ ግዥ፣ ሎት 2 የቆርቆሮ አጥር ግንባታ እና ሌሎች ማቴርያል ወይም እቃዎች ግዥ፣ ሎት 3 የባህርዛፍ ሽያጭ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛትና መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ሎት 1 የቆርቆሮ አጥር ግንባታ የእጅ ዋጋ ግዥ፣ ሎት 2 የቆርቆሮ አጥር ግንባታ እና ሌሎች ማቴርያል ወይም እቃዎች ግዥ፣ ሎት 3 የባህርዛፍ ሽያጭ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛትና መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ሎት 1 እና ሎት 2 የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡ ሎት 3 የባህርዛፍ ሽያጭ ማንኛውም ሰው መወዳደር ይችላል፡፡
1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የሚመለከተው የንግድ ፈቃድ ያላቸው።
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው።
3. የግዥው የብር መጠን 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለበት ለዚህም ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፡፡
4. ተጫራቾች ከሎት 1 እና 2 የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200 ብር በመክፈል ከ10 /09/2018ዓ/ም እስከ 25/09/2018ዓ/ም ዘወትር በስራ ሰአት ቢሮ ቁጥር 05 ወይም 19 መግዛት ይችላሉ፡፡
6. ጨረታው በ25/09/2018 ዓ/ም 3:35 ታሽጎ በ4፡00 ሰአት ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ቀኑ በዓል ከሆነ የሚቀጥለው ቀን ይከፈታል፡፡
7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሎት 1 የሞሉትን ጠ/ዋጋ 2%፣ ለሎት 2 የሞሉትን ጠ/ዋጋ 1%፣ ለሎት 3 የሞሉትን ጠ/ዋጋ 10% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ በአማርኛ የተተረጎመ የባንክ ዋስትና ማቅረብ አለበት፡፡
8. ኮሌጁ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። አሸናፊ የሚለየው በድምር ዋጋ ነው፡፡
9. ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ ጎ/መ/ት/ኮሌጅ ቢሮ ቁጥር G1 በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0581121634 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ
