ሕዳሴ ቴሌኮም አክሲዮን ማህበር የፋይናንስ አማካሪ አገልግሎት ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የፋይናንስ አማካሪ አገልግሎት ግዥ
ለ2ኛ ግዜ የወጣ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር፡RE-LT/HT/HO/05/2026
- ሕዳሴ ቴሌኮም አክሲዮን ማህበር የፋይናንስ አማካሪ አገልግሎት ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከግንቦት 20 ቀን 2018ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 09 ቀን 2018ዓ.ም ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡00-6፡00 እንዲሁም ከሰዓት በኋላ ከ7፡30-10፡00 ድረስ ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡30-6፡00 “ሕዳሴ ቴሌኮም አ.ማ” ጠመንጃ ያዥ ንግድ ባንክ አጠገብ ቴሌ ጋራዥ ግቢ ውስጥ 2ኛ ፎቅ ቢሮቁጥር 211 በመቅረብ የማይመለስ ብር00 /ሶስት መቶ/ በመክፈል እና የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የታክስ ክሊራንስ ሰርተፍኬት፣ እና የቫት ምዝገባ ሰርተፍኬት ፎቶ ኮፒውን በመያዝ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት፡-
- አንድ ዋና /Original/ የጨረታ ሰነድ ለብቻው በሰም በታሸገ ፖስታ ታሽጐ፣
- አንድ ቅጂ /Copy/ የጨረታ ሰነድ ለየብቻው በሰም በታሸገ ፖስታ ታሽጐ እንዲሁም፣
- ሁሉም በአንድ ላይ በትልቅ ፖስታ ውስጥ ተካቶ በሰም የታሸገ መሆን አለበት፣
- በዋናውና በቅጂው መካከል ልዩነት ቢፈጠር ዋናው ተቀባይነት ይኖረዋል፡፡ ተጫራቾች የሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ ላይ ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፡፡ የተሰረዘ ሰነድ በፊርማ መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡበትን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 10,000.00 /አስር ሺህ ብር/ የባንክ ክፍያ ማዘዣ /C.P.O/ ብቻ ለሕዳሴ ቴሌኮም አ.ማ በሚል ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ የመጨረሻ ቀን ሰኔ 9 ቀን 2018ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ቢሮ ቁጥር 211 ሲሆን፣ ጨረታው የሚከፈተው በዚሁ ቀን ሰኔ 09ቀን 2018ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 211 ይሆናል::
- ከላይ የተገለጸውን መመሪያ ያልተከተሉ ተጫራቾች ወዲያውኑ ከጨረታ ውድድሩ ውጪ እንደሚሆኑ እንገልጻለን፡፡
- ተጫራቾች ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0968135675 ወይም 0968271291 መጠቀም ይችላሉ፡፡
- ሕዳሴ ቴሌኮም አ.ማ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ሕዳሴ ቴሌኮም አክሲዮን ማህበር
