የአርባምንጭ ማረሚያ ተቋም በህግ ጥላ ሥር ለሚገኙ ህግ ታራሚዎች ለ2019 በጀት ዓመት የሚሆን የተለያየ ዓይነት እህልና የማገዶ እንጨት በግልጽ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በማሳወጅ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የአርባምንጭ ማረሚያ ተቋም በህግ ጥላ ሥር ለሚገኙ ህግ ታራሚዎች ለ2019 በጀት ዓመት የሚሆን የተለያየ ዓይነት እህልና የማገዶ እንጨት በግልጽ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በማሳወጅ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚህ መሰረት፡
1. የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ
2. የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት
3. የግብር ከፋይ ምዝገባ ምስክር ወረቀት
4. የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ምስክር ወረቀት እና ሌሎች ይጠቅመኛል ካሉት መረጃ ጋር አያይዞ ማቅረብ የሚችል ሆኖ ከላይ በተገለጸው ዝርዝር መሰረት ተጫራቾች፡-
የጨረታውን ዝርዝር የሚገልጽ ሰነድ አርባምንጭ ማረሚያ ተቋም ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 3 በመቅረብ የማይመለስ 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ ከፍሎ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000.00 /አሥር ሺህ/ ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ አርባምንጭ ማረሚያ ተቋም ገቢ በማድረግ የደረሰኙን ኮፒ ፖስታ ውስጥ በማስገባት የጨረታውን ሰነድ በታሸገ ፖስታ ኦሪጅናልና ኮፒ በመለየት ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት የሚችሉ መሆኑን ይገልፃል።
ጨረታው የሚከፈተው በ16ኛው ቀን 4፡30 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን 5፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
የጨረታው መክፈቻ ቀን ቅዳሜ፤ እሁድና የበዓላት ቀን ላይ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል።
በጨረታው አሸናፊ የሆነው ያሸነፈውን እህልና ማገዶ እንጨት ማሸነፉ ሲረጋገጥ ቀርቦ ውልበመግባት በራሱ ወጪ እስከ ማረሚያ ተቋም ግቢ ድረስ በማምጣት ያስረክባል።
ማሳሰቢያ፡- የተጫራቾች መገኘት አለመገኘት የጨረታውን መክፈቻ ሂደት አያስተጓጉልም።
ተቋሙ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡- ስልክ ቁጥር 0468810049 እና 0468810093 ላይ ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የአርባምንጭ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም
