Tender Detail

Tender Details

  • Company በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የአርባምንጭ ማረሚያ ተቋም
  • Address አርባምንጭ : ደቡብ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 046 881 0049
  • Website
  • Deadline13 Jun 2026, 10:30 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price200.00
  • opening date2026-06-15 11:00:00
  • Categories Firewood

የአርባምንጭ ማረሚያ ተቋም በህግ ጥላ ሥር ለሚገኙ ህግ ታራሚዎች ለ2019 በጀት ዓመት የሚሆን የተለያየ ዓይነት እህልና የማገዶ እንጨት በግልጽ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በማሳወጅ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።


የጨረታ ማስታወቂያ

 

የአርባምንጭ ማረሚያ ተቋም በህግ ጥላ ሥር ለሚገኙ ህግ ታራሚዎች 2019 በጀት ዓመት የሚሆን የተለያየ ዓይነት እህልና የማገዶ እንጨት በግልጽ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በማሳወጅ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

በዚህ መሰረት፡

1.     የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ

2.     የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት

3.     የግብር ከፋይ ምዝገባ ምስክር ወረቀት

4.     የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ምስክር ወረቀት እና ሌሎች ይጠቅመኛል ካሉት መረጃ ጋር አያይዞ ማቅረብ የሚችል ሆኖ ከላይ በተገለጸው ዝርዝር መሰረት ተጫራቾች፡-

የጨረታውን ዝርዝር የሚገልጽ ሰነድ አርባምንጭ ማረሚያ ተቋም ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 3 በመቅረብ የማይመለስ 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ ከፍሎ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።

የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000.00 /አሥር ሺህ/ ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ አርባምንጭ ማረሚያ ተቋም ገቢ በማድረግ የደረሰኙን ኮፒ ፖስታ ውስጥ በማስገባት የጨረታውን ሰነድ በታሸገ ፖስታ ኦሪጅናልና ኮፒ በመለየት ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ከጠዋቱ 230 እስከ 1130 ሰዓት ድረስ ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት የሚችሉ መሆኑን ይገልፃል።

ጨረታው የሚከፈተው 16ኛው ቀን 430 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን 500 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።

የጨረታው መክፈቻ ቀን ቅዳሜ፤ እሁድና የበዓላት ቀን ላይ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል።

በጨረታው አሸናፊ የሆነው ያሸነፈውን እህልና ማገዶ እንጨት ማሸነፉ ሲረጋገጥ ቀርቦ ውልበመግባት በራሱ ወጪ እስከ ማረሚያ ተቋም ግቢ ድረስ በማምጣት ያስረክባል።

 

ማሳሰቢያ፡- የተጫራቾች መገኘት አለመገኘት የጨረታውን መክፈቻ ሂደት አያስተጓጉልም።

ተቋሙ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ፡- ስልክ ቁጥር 0468810049 እና 0468810093 ላይ ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ።

 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የአርባምንጭ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም

Save Tender