የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፒያሳ የሚገኘውን የኤሌክትሪክ ህንፃ ለሱቅና ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ክፍሎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል፡፡
ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ኢኤአ/ፍፋግ-ግጨ/036/2018
ተቋማችን ፒያሳ የሚገኘውን የኤሌክትሪክ ህንፃ ለሱቅና ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ክፍሎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል፡፡
|
ሎት |
የዕቃው ዓይነት |
ብዛት |
የጨረታ ማስከበሪያ (CPO) |
የጨረታ መዝጊያ ቀን እና ሰዓት |
የጨረታ መክፈቻ ቀን እና ሰዓት |
|
1 |
የሱቅ ኪራይ አገልግሎት |
|
50,000.00 |
ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት |
ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ሰዓት |
1. ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራ የዘመኑ ግብር የተከፈለበት የንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የታደሰ የታክስ ክሊራንስ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል ፤የግብር ከፋይ መለያ ቁጥርያለው በጨረታው መሳተፍ ይችላል፡፡
2. ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት ሜከሲኮ ንብ ባንክ በሚገኝበት ዋናው መስሪያ ቤት 10ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው ፍሊትና ፋሲሊቲ ግዥ ክፍል በመምጣት የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000068699332 በመክፈል ሶፍት ኮፒ በኢሜይል አድራሻቸው መውሰድ ይችላሉ፡፡
3. አድራሻ፡- ሜክሲኮ ንብ ባንክ በሚገኝበት ዋናው መስሪያ ቤት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋናው መስሪያ ቤት 10ኛ ፎቅ ፍሊትና ፋሲሊቲ ግዥ ክፍል ስልክ ቁጥር 011-156-01-48
4. ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና < Ethiopian Electric Utility > በሚል መሆን ይኖርበታል፤
5. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ ከላይ አስከ ተጠቀሰው ቀን፤ ሰዓት እና አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፤
6. ጨረታው ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት /ባይገኙም⁄ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡
7. ተቋሙ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
