ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ውል ይዞ ለሚገናባው ለፌደራል ገቢዎች ባ/ዳር ቅርንጫፍ ግንባታ ፕሮጀከት የTempered Glass Work አቅርቦትና ገጠማ ስራ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት እና ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 50/2018
የዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ውል ይዞ ለሚገናባው ለፌደራል ገቢዎች ባ/ዳር ቅርንጫፍ ግንባታ ፕሮጀከት የTempered Glass Work አቅርቦትና ገጠማ ስራ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት እና ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን፤
1. በዘርፉ ለዘመኑ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድና፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) እና የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት እና የንግድ ፈቃድ ለማደስ ግብር ስለመከፈላቸው የሚሰጥ ማስረጃ ያለው ያላት፤ አቅርቦት እና ገጠማ ሥራ ከዚህ በፊት ለመስራታቸው ህጋዊ ከሆነ ተቋም የመልካም ስራ አፈጻጸም ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፤
2. የጨረታ ማስከበሪያ ቫትን ጨምሮ የጠቅላላ ዋጋውን 2% በባንከ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.አ (CPO) ወይም/unconditional bank guarantee/ በሁኔታ ላእ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያስ ይኖርበታል፣
3. የጨረታ ሰነዱ ባ/ዳር ከተማ ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ቀበሌ 11 እና አ/አበባ ለገሀር አመልድ ህንፃ 7ኛ ፎቅ በሚገኘው ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር ዐ2 የማይመለስ ብር 3ዐዐ /ሶስት መቶ/በመከፈል ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት መውስድ ይችላሉ፤
4. የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀናት ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናልና ኮፒውን በመለየት በተለያዩ ፖስታዎች በጥንቃቄ በማሸግ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሠዓት ድረስ ብቻ ባ/ዳር ዋናው መ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ በእለቱ 8፡ዐዐ ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ 8፡3ዐ ይከፈታል፡፡ 15ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን እስከ ቀኑ 8፡ዐዐ ሠዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው የሚከፈተው ባህር ዳር ዋናው ቢሮ አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 የማን/ግብ ግዥ እና አቅርቦት ኬዝ ቲም ቢሮ ከፍል ነው።
5. ውድድሩ በሎት /በጥቅል ዋጋ የሚታይ ይሆናል፤ ዝርዝር የጨረታ መመሪያው እና የውል ይዘቱ በጨረታ ሰነዱ ውስጥ የተገለፀ ስለሆነ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በማንበብ ዋጋቸውን በጨረታ መመሪያው መሰረት በሰነዱ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ በመሙላት ማቅረብ አለባቸው፡፡
6. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው፡፡ ለማንኛውም ተጨማሪ ማብራሪያ ስልክ ባ/ዳር 058-218-05-38/09-18-01-06-17/09-13-27-60-57
አዲስ አበባ:- 011-126-56-52/5145/0912085639
ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን
