ኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት የፅዳት አገልግሎት ግዥ ግልፅ ጨረታ ለማዕከሉና ለመስቀል አደባባይ ፋስሊቲ ማኔጅመንት ለቢሮ ፣ የተሸከርካሪ ማቆሚያ ፓርኪንግ እና ፕላዛ ላይ የፅዳት አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ አገልግሎት ማግኘት ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ የፅዳት አገልግሎ ግዥ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡ 023/2018
ኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት የፅዳት አገልግሎት ግዥ ግልፅ ጨረታ ለማዕከሉና ለመስቀል አደባባይ ፋስሊቲ ማኔጅመንት ለቢሮ ፣ የተሸከርካሪ ማቆሚያ ፓርኪንግ እና ፕላዛ ላይ የፅዳት አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ አገልግሎት ማግኘት ይፈልጋል፡፡
- በዘርፉ የተሰማራና ከድርጅታችን ጋር በማንኛውም ሥራ ውል ፈጽሞ እየሰራ ያልሆነ፣
- ከማንኛውም ዕዳና ዕገዳ ነፃ የሆነ ድርጅት ፣
- ተጫራቾች የዘመኑን ግብር ከፍለው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምሰክር ወረቀት፣የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የTIN ሰርተፊኬት፣ማስረጃዎች ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ጨረታው ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማለትም ከግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ/ም እስከ ከሰኔ 07 ቀን 2018 ዓ.ም ለ8 ተከታታይ የስራ ቀናት አየር ላይ የሚቆይ ሲሆን በ 9 ኛው ቀን ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡30 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከሰዓት 8፡35 ሰዓት የኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት መ/ቤት ተጫራቾች እና ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት ብር 500/አምስት መቶ/ ከፍለው መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት በባንክ በተረጋገጠ ትዕዛዝ (CPO) ብር 100,000.00(መቶ ሺህ ብር) ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያቸዉን እና የጨረታ ማስከበሪያዉን በተለያየ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ተጫራች ድርጅቶች ለሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ለማዕከሉና ለመስቀል አደባባይ ፋስሊቲ ማኔጅመንት ለየብቻ በትክክል ሞልተው በግልፅ ማስቀመጥ አለባቸው፡፡
- ይህ ጨረታ በድርጅቱ የግዥ መመሪያ መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
- የጨረታዉ አሸናፊ አሸናፊነቱ በጽሁፍ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በ 3 ቀናት ዉስጥ የጠቅላላ ዋጋዉን 10% የዉል ማስከበሪያ ያለቅድመ ሁኔታ ለገዥ የሚከፈል (Unconditional Bank Guarantee) በማሰራት ዉል የመያዝ ግዴታ ይኖርበታል፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በዚህ ጨረታ አይገደድም ወይም ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ዝርዝር የጨረታ ሰነዱን መስቀል አደባባይ በሚገኘው የኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ማሳሰቢያ፡-የፋይናንስ ውድድሩ ለማዕከሉና ለመስቀል አደባባይ ፋስሊቲ ማኔጅመንት ለየብቻ በሚቀርብ ጠቅላላ ዋጋ ቫትን ጨምሮ በሚሞሉት መሰረት ይሆናል፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን 0115151693 መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት
