የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በ2018 በጀት ዓመት የማተሚያ ማሽኖችን ከቅድመ ህትመት እስከ ድህረ ህትመት (sheet fed offset press, folding machine, paper cutting machine, perfect binding machine, double saddle stitcher, laminating machine, heavy duty printer, Thermal ctp) (ተከላ፣ ሥራ ማስጀመር፣ ሥልጠና እና
ዓለም አቀፍ የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 001/2018
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በ2018 በጀት ዓመት የማተሚያ ማሽኖችን ከቅድመ ህትመት እስከ ድህረ ህትመት (sheet fed offset press, folding machine, paper cutting machine, perfect binding machine, double saddle stitcher, laminating machine, heavy duty printer, Thermal ctp) (ተከላ፣ ሥራ ማስጀመር፣ ሥልጠና እና ፍተሻን ጨምሮ በዓለም አቀፍ የግልጽ ጨረታ የግዥ ዘዴ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም:- ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ ይችላሱ፡፡
· በዘርፉ የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያለው
· የንግድ ምዝገባ
· የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፍኬት
· የቫት ሰርተፍኬት
· በመንግስት ግዥ በአቅራቢነት የተመዘገበ
ለጨረታ ማስከበርያ መጠን 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ ብር) ወይንም በውጭ ሀገር መገበያያ ገንዘብ (የአሜሪካ ዶላር፣ የእንግሊዝ ፓውንድ፣ ወይም ዩሮ) በሲፒኦ ወይም ቢድ ቦንድ ወይም ለጥቃቅንና አነስተኛ ከአደራጃቸው አካል የሚሰጥ የዋስትና ደብዳቤ በማያያዝ ይህ ጨረታ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 45 ተከታታይ ቀናት አንደኛ ፎቅ በሚገኘው አቅርቦት መምሪያ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ቴክኒካል ዶከመንት ዋና እና ቅጂ እንዲሁም የሚወዳደሩበትን ዋጋ ዋና እና ቅጂ በሚል በጉልህ በሚታይ መልኩ በመጻፍና የሚወዳደሩበትን በፖስታዎቹ ላይ በመግለጽ በአራት የተለያየ ፖስታ በማሸግ ማስገባት የሚኖርባቸው ሲሆን የጨረታ ማስከበሪያ ቴክኒክ ዋና ሰነድ ፖስታ ውስጥ ተያይዞ መገኘት አለበት፡፡
· በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 45 ተከታታይ ቀናት የማይመለስ 100 ብር በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
· ስርዝ ድልዝ ያለውና ያልተፈረመ እንዲሁም በጉልህ የማይታይ አጠራጣሪ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
· ጨረታው በ46ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ 4፡30 በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አቅርቦት መምሪያ 1ኛ ፎቅ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ሲሆን የተጫራቹ አለመገኘት ጨረታውን ከመከፈት አያስተጓጉለውም፡፡ የጨረታ መክፈቻው ቀን እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣይ ባለው የስራ ቀን የሚከፈት ይሆናል፡፡
· ድርጅታችን አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- አራት ኪሎ ከብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ፊት ለፊት
E-mail: procurement@press.et
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
