በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ግብርና ቢሮ የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ በ2018 ትምህርት ዘመን ለሶስት ተከታታይ ዓመታት ያስተማራቸውን ተማሪዎችን በቀን ዘ/11/2018 ዓ/ም ለሚያስመርቀው የምረቃ ፕሮግራም በዕለቱ ለታዳሚዎች በሚቀረበው የኮሌጁ ዓመታዊ ሥራ አፈጻጸም የግንዛቤ ማስጨበጫ _ እና _ ለተመራቂ ተማሪዎች የሥራ መመሪያ የሚሰጡ ክቡር እንግዶችና ለኮሌጁ መምህራንና አስ/ር ሠራተኞች የሚሆን
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር 008/ 2018
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ግብርና ቢሮ የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ በ2018 ትምህርት ዘመን ለሶስት ተከታታይ ዓመታት ያስተማራቸውን ተማሪዎችን በቀን ዘ/11/2018 ዓ/ም ለሚያስመርቀው የምረቃ ፕሮግራም በዕለቱ ለታዳሚዎች በሚቀረበው የኮሌጁ ዓመታዊ ሥራ አፈጻጸም የግንዛቤ ማስጨበጫ _ እና _ ለተመራቂ ተማሪዎች የሥራ መመሪያ የሚሰጡ ክቡር እንግዶችና ለኮሌጁ መምህራንና አስ/ር ሠራተኞች የሚሆን የሪፍሬሽመንት አገልግሎት ግዥ በግልጽ ጨረታ መስፈርቱን የሚያሟሉትን አወዳድሮ ለመግዛትና ወጪውም የ2019 በጀት ዓመት አካል እንድሆን ይፈልጋል። በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚችሉ ድርጅቶች፡፡
1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን የግብር ግዴታቸውን የተወጡ፣ የተ.እ.ታ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ የቲን ሰርተፍኬት /የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር/ ያላቸው፣ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው፣ በመስተንግዶ ሥራ የመልካም ስራ አፈጻጸም ማቅረብ የሚችል።
2. የሪፍሬሽመንት አገልግሎት ጊዜ በምረቃው ዕለት በኮሌጅ ግቢ ውስጥ በበቂ ሁኔታ ድንኳን ተከሎ የሚያቀርብ ይሆናል።
3. ተጫራቾች ዝርዝር የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጅምሮ ዘውትር በሥራ ሰዓት ለጨረታ ዶክመንቱ የማይመለስ ብር 300.00/ሶስት መቶ ብር/ በሶዶ ግብርና ኮሌጅ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተከፍቶ በሚገኘው አካውንት ቁጥር 1000018208443 በማስገባት አድቫይስ በመያዝ ወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ ግ/ክ/ን/አስ/ር ቡድን ቢሮ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
4. የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሰከረለት ሲፐኦ ብር 30,000.00/ሰላሳ ሺህ/ ከጨረታው ሰነድ ኦርጅናል ጋር አሽገው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
5. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያውን ሰነድ አንድ ኦርጅናልና 1 የኦርጅናሉን ፎቶ ኮፒ ለየብቻ በስም በታሸገ ኤምቨሎፕ ሙሉ አድርሻቸውን በመጥቅስ ለዚሁ በተዘጋጀው ጨረታ ሳጥን ውስጥ መስገባት አለባቸው።
6. የጨረታው ሳጥንይህማስታወቂያ ከወጣበትቀንጀምሮ ከ15ተከታታይቀናትቀጥሎ በሚውለው 16ኛ የሥራ ቀን 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ ተጫራቾችና ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 4፡30 ሰዓት ላይ ወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ ግ/ክ/ን/አስ/ር ቡድን ቢሮ ይከፈታል።16ኛው የሥራ ቀን ካልሆነ ቀጥሎ በሚውለው የሥራ ቀን ይከፈታል። 7. ተጫራቾች በሚያቀርቡት ነጠላ ዋጋ ላይ የማይነበብና ሰርዝ ድልዝ ያለው መሆን የለበትም፡፡ 8. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በከፈልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0465513984/0916834217/ መደወል ይቻላል።
ወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ
