የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ከልል መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን ለ2019 በጀት ዓመት የከልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በአዲስ መልከ ለተዋቀረው የማርሽ ባንድ የሚያስፈልጉ ልዩ ልዩ የማርሽ ባንድ የሙዚቃ መሳሪያዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የግዥ ማስታወቂያ ቁጥር(ሶስት) 03/2018 ዓ.ም
የተስያዩ አይነት ዕቃዎች ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ከልል መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን ለ2019 በጀት ዓመት የከልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በአዲስ መልከ ለተዋቀረው የማርሽ ባንድ የሚያስፈልጉ ልዩ ልዩ የማርሽ ባንድ የሙዚቃ መሳሪያዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች -
1. ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው:
♦ የዘመኑ ግብር የተከፈለበት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል
♦ በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለው
♦ የቅራቢነት ምስከር ወረቀት ያለው
♦ የታክስ ከፋይነት ምዝገባ የምሥከር ወረቀትና ግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ወይም ቲን ሰርቲፍኬት ያለው
♦ የተጨማሪ እሴት ታከስ /ቫት ተመዝጋቢ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል
♦ የትብብር ደ/ቤ ማቅረብ የሚችል
2. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና/Bid Bond/ ለሚያቀርቡት የዕቃዉን ጠቅላላ ዋጋ 2% /CPO/ ወይም ሌተር አፍ ከሬዲት ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
3.ተጫራቾች አንድ ተጫራች የሰጠውን ዋጋ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት የተከለከለ ነው የተሞላው ዋጋ ከዘጠና ቀናት(90) በታች መሆን የለበትም፡፡
4. ተጫራቾች በሰነዶቻቸው ላይ ስማቸውን ሙሉ አድራሻቸውንና ፊርማቸውን አሟልተው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
5.የቴከኒካል ስፔስፍኬሽን እና የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በቅጂ ማቅረብ አለባቸዉ::
6. ተጫራቾች ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር50/ሃምሳ ብር/ በመክፈል ለ15 ተከታታይ ቀናት እስከ ቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ከልል መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን ግዥና ፋይ/ን አስተደደር ዳይሬክቶሬት በመምጣት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
7. ተጫራቾች የመጫረቻ ዋጋቸውን በጨረታ ሰነድ ላይ በተጠቀሰው መሠረት በግልጽ ማቅረብ አለባቸው፡፡
8. ጨረታ የሚከፈተው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከ15ኛው ቀን በኋላ በቀጣዩ የሥራ ቀን ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡ ጨረታዉም በዚሁ ዕለት ከሰዓት በኋላ 08፡00 ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኮሚሽኑ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
9. ኮሚሽኑ ከአሸናፊ ተጫራቾች ጋር ውል በሚዋዋልበት ጊዜ 20% የመጨመር ወይንም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
10. ኮሚሽኑ ከአሸናፊ ተጫራቾች ጋር ውል ከተዋዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ ስድስት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ 25% የመጨመር መብት አለው፡፡
11. ኮሚሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀው::
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልከ ቁጥር ሞባይል ቁጥር 0910062954 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ፖሲስ ኮሚሽን
