ፀሐይ ኢንሹራንስ አ.ማ ዋና መሥሪያ ቤቱን በአሁኑ ቦታው (ቦሌ ድልድይ የቀድሞው ብራስ ሆስፒታል ፊት ለፊት) ከሚገኘው ቢሮ አዲስ ወዳስገነባው ዋና መ/ቤት አድራሻ (አዲስ አበባ ሬስቶራንት ፊት ለፊት፣ ደጃዝማች ውቤ አካባቢ) ለማዛወር ይፈልጋል::
ፀሐይ ኢንሹራንስ አ.ማ.
የጨረታ ማስታወቂያ፡
የቢሮ ዕቃ ማዛወር አገልግሎት ግዥ
ፀሐይ ኢንሹራንስ አ.ማ ዋና መሥሪያ ቤቱን በአሁኑ ቦታው (ቦሌ ድልድይ የቀድሞው ብራስ ሆስፒታል ፊት ለፊት) ከሚገኘው ቢሮ አዲስ ወዳስገነባው ዋና መ/ቤት አድራሻ (አዲስ አበባ ሬስቶራንት ፊት ለፊት፣ ደጃዝማች ውቤ አካባቢ) ለማዛወር ይፈልጋል::
በዚሁ መሠረት፥ ኩባንያው የቢሮ ዕቃዎችን (ጠረጴዛዎች፣ ወንበሮች፣ የኮምፒውተርና የሰርቨር ዕቃዎችን ወዘተ) እና የተለያዩ የኩባንያውን ሰነዶች በጥንቃቄ በማሸግ፣ በመጫን፣ በማጓጓዝ እና በማውረድ/በማደራጀት የተረጋገጠ ልምድ ያላቸውን ብቁ ድርጅቶች በዚህ ክፍት ጨረታ እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡
ከተጫራቾች የሚጠየቁ መስፈርቶች፡
1. ተጫራቾች ሀጋዊ እና የታደሰ የንግድ ፈቃድ ሊኖራቸው እና የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን አለባቸው::
2. ተጫራቾች ተመሳሳይ ስራዎችን በመስራት የ5 ዓመት ልምድ እና አቅም እንዳላቸው ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው::
3. ተጫራቾች አስፈላጊ የሆኑ የማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን እና የማሸጊያ ቁሳቁሶችን የማቅረብ አቅም ሊኖራቸው ይገባል::
4. ተጫራቾች ስራውን ለማጠናቀቅ የሚፈጅባቸውን ጊዜ የሚያሳይ የሥራ መርሃ ግብር ማቅረብ አለባቸው::
5. የጨረታ ማስከበሪያ ተጫራቾች 50,000.00 ብር (ሃምሳ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (CPO) ወይም ያለ ቅድመ ሁኔታ በሚፈጸም የባንክ ዋስትና (Bank Guarantee) ማቅረብ አለባቸው::
6. አገልግሎት ሰጪው በእንቅስቃሴው ሂደት ለሚደርስ የሰነድ መጥፋት ወይም ጉዳት የኢንሹራንስ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅበታል::
የጨረታ ሂደት፡
· የጨረታ ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ቦሌ ድልድይ የቀድሞ ብራስ ሆስፒታል ፊት ለፊት በሚገኘው 3ኛ ፎቅ የኩባንያው የፋይናንስ መምሪያ በመቅረብ፣ የማይመለስ 200.00 ብር (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
· የጨረታ ማስረከበሪያ፡ የተሟላ የጨረታ ሰነድ በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
· የጨረታ መክፈቻ፡ ጨረታው ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
· የኩባንያው መብት፡ ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
· የቢሮቹን ጉብኝት፡ ተጫራቾች የሁለቱንም ሕንፃዎች አቀማመጥ እና የሚዛወሩ ዕቃዎችን አይነትና መጠን ለመገምገም የሚያስችል የቅድመ-ጨረታ የጉብኝት ፕሮግራም ከ22/10/2018 -28/10/2018 በስራ ሰዓት ማየት ይቻላል።
አድራሻ፡- ፀሐይ ኢንሹራንስ አ.ማ ዋና መሥሪያ ቤት ቦሌ ድልድይ፣ የቀድሞ ብራስ ሆስፒታል ፊት ለፊት
ስልክ፡- +251 111 119 70 / +251 116 50 66 30
