ፀደይ ባንክ አክሲዮን ማህበር ያገለገሉ የተለያዩ እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል::
የጨረታ ማስታወቂያ
ፀደይ ባንክ አክሲዮን ማህበር ያገለገሉ የተለያዩ እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል:: ስለሆነም ከዚህ በታች የቀረበውን የጨረታ መመሪያ የሚያሟላ ማንኛውም ፍላጎት ያለው መወዳደር የሚችል መሆኑን እንገልጻለን::
የጨረታው መመሪያ
Ø በጨረታው በሁሉም ዓይነቶች ወይም በከፊል መወዳደር ይቻላል::
Ø ተጫራቾች ለሚሳተፋባቸው የእቃ አይነት የሚገዙበትን ዋጋ በዋጋ መሙያ ፎርማቱ ላይ መሙላት ይገባቸዋል :: በነጠላ ዋጋና በድምሩ ልዩነት ካለ ነጠላ ዋጋው የሚያዝ ይሆናል:: ዋጋ ሲሞላ ስርዝ ካለ ፊርማ ሊኖረው ይገባል:: ሆኖም ግን ስርዝ ድልዝ ከበዛበትና ግልፀኝነት ከጐደለው ተወዳዳሪው ከጨረታው ይሠረዛል::
Ø ለጨረታ ማስከበሪያ የሚውል የአጠቃላይ ዋጋውን 2% ሲፒኦ /CPO/ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ የ80 ቀን በፀደይ ባንክ ትክክልኛ ስም በማሰራት ማስያዝ ይኖርበታል።
Ø ጨረታው ወቅቱ ተጠናቆ ያላቀረበ ማንኛውም ማስረጃ ተቀባይነት አይኖረውም::
Ø የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በአየር ላይ ከዋለበት ከ24/10/2018 ዓም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በስራ ስዓት ከሰኞ እስከ አርብ 2:00-11:00 እና ቅዳሜ እስከ 6:00 የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ ለገሃር ቅርንጫፍ ገቢ በማድረግ ሰንጋተራ በሚገኘዉ የባንኩ ህንፃ 16ተኛ ፎቅ ግዥ ክፍል ሰነዱን መግዛት ይችላሉ::
Ø የጨረታውን ሰነድ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 3/11/2018 ዓ.ም ቀን አዲስ አበባ ሰንጋተራ በሚገኘው ፀደይ ባንክ ዋና መ/ቤት 16ተኛ ፎቅ ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ድረስ ለዚህ ተግባር ከተዘጋጀው ሳጥን በኢንቨሎፕ በማሸግ የተወዳደሩበትን የጨረታ አይነት፣ የተወዳዳሪዉን ስም እና አድራሻ በመፃፍ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል::
Ø ጨረታው በዚህ እለት ከቀኑ 4፡30 ጀምሮ ተጫራቾቸ ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በግልፅ ይከፈታል::
Ø ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
አድራሻ፡ ሰንጋ ተራ ፀደይ ባንክ ዋና መ/ቤት
ስ.ቁ 0111-30-54-88/0932169386
