የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለምስራቅ ኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ፈጥኖ ደራሽ (ድሬዳዋ) ቢሮና ካምፕ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚውል Supply and fix Diesel Generator ግዥ ለመፈፀም ተጫራቾችን ከዚህ በታች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር DCE/SF/94/2026
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለምስራቅ ኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ፈጥኖ ደራሽ (ድሬዳዋ) ቢሮና ካምፕ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚውል Supply and fix Diesel Generator ግዥ ለመፈፀም ተጫራቾችን ከዚህ በታች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
|
ተ/ቁ
|
የዕቃው ዓይነት
|
ፕሮጀክት
|
የጨረታ ቁጥር
|
የጨረታው መዝጊያ ቀን እና ሰዓት
|
የጨረታው መክፈቻ ቀን እና ሰዓት
|
የጨረታ ማስከበሪያ ብር
|
|
1
|
Generator
|
ድሬዳዋ
|
DCE/ SF/94/2026
|
ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡15 ሰዓት
|
ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም 04፡30 ሰዓት
|
300,000 ብር
|
ስለሆነም፡-
1. ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩ፤ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ እና በጨረታ ለመወዳደር የሚያስችላቸው ከግብር ሰብሳቢው ባለስልጣን የተሰጠ የታደሰ ታክስ ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
2. ተጫራቾች ከላይ በሰንጠረዡ በተገለፀው መሰረት የጨረታ ማስከበሪያ ቦንድ (Bid Bond) 120 ቀን ፀንቶ የሚቆይ ማቅረብ ይኖርበታል። የጨረታ ማስከበሪያው እንደተጫራቹ ምርጫ በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ በባንክ ዋስትና (unconditional Bank Guarantee) ወይም በባንክ የተሰጠ የተረጋገጠ ቼክ (CPO) መቅረብ ይኖርባቸዋል። የመድን ድርጅቶች ዋስትና ተቀባይነት አይኖረውም።
3. አንድ ተጫራች መወዳደር የሚችለው በአንድ ዓይነት ምርት (ብራንድ) ብቻ ነው። በአማራጭ የቀረበ ዋጋ ተቀባይነት አይኖረውም።
4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር ለእያንዳንዱ ጨረታ ቁጥር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ዋና መ/ቤት አዲሱ ቢሮ ቃሊቲ ቶታል ማደያ ዝቅ ብሎ የቀድሞ መኮድ ግቢ ውስጥ
5. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የጨረታ ቴክኒካል ሰነድ እና ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ ከላይ በሰንጠረዡ በተገለፀው ቀንና ሰዓት በኢንተርፕራይዙ የግዥና አቅርቦት አስተዳደር መምሪያ ቢሮ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
6. ጨረታው በሰንጠረዡ በተገለፀው መሠረት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
7. ኢንተርፕራይዙ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ቃሊቲ ቶታል ማደያ ዝቅ ብሎ የቀድሞ መኮድ ግቢ
የቀጥታ ስልክ ቁጥር 09 11 17 17 51/ 09 13 29 72 97
E-mail አድራሻ Info@dce-et.com
የድረ ገፅ አድራሻ www.dce-et.com
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ
