በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታ ማማከር ድርጅት ልዩ ልዩ መሳሪያዎች እና እቃዎች የሌቭሊንግ መሳሪያ ከነሙሉ አከሰሰሪውና የኤሌክትሪክእና ኤሌክትሮኒከስ ተያያዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር/ኮ/ዲ/ግ/ማ/ድ/ግ/ቸ/ቁ/23/2018
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታ ማማከር ድርጅት ልዩ ልዩ መሳሪያዎች እና እቃዎች ሎት 1.የሌቭሊንግ መሳሪያ ከነሙሉ አከሰሰሪው ሎት 2.የኤሌክትሪክእና ኤሌክትሮኒከስ ተያያዥ ልዩ ልዩ እቃዎች ሎት 3.ለግንባታና ለፎቶግራፊ ስራ የሚውል ድሮን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም፦
1. በዘርፉ የተሰማሩ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ ለመሆናቸው ማስረጃ ኮፒ አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ ድርጅቶችና ግለሰቦች የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 300 (ሦስት መቶ ብር) በመከፈል በኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታ ማማከር ድርጅት ቃሊቲ ማሰልጠኛ ፊት ለፊት C.R.D.A አጠገብ በመቅረብ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
2. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ ሎት ለየብቻ በመለያየት 70,000.00 ብር/ሰባ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ (CPO) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የ90 ቀናት የባንክ ዋስትና (un-conditional bid bond guarantees) ከሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሰነድ ጋር በማያያዝ በየሎቱ የቴከኒክ እና ፋይናሻል ሰነድ በሁለት ፖስታ በመለያየት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
3. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት በአየር ላይየሚቆይ ሆኖ በአሥራ አንደኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ እለት ከጠዋቱ 4፡30 በግዥ ዳይሬከቶሬት ተሳታፊዎች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ሲሆን እለቱ የስራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን የሚከፈት ይሆናል፡፡
4. ኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታ ማማከር ድርጅት የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታ ማማከር ድርጅት ቃሊቲ ማሰልጠኛ ፊት ለፊት ከሲ.አር.ዲ.ኤ አጠገብ
ስልክ ቁጥር፡- 09 30 48 90 18 / 09 21 02 25 81
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንስትራክሽን
ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት
