Tender Detail

Tender Details

  • Company የሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን
  • Address Addis Ababa Ethiopia, Phone: 0984820007
  • Website
  • Deadline05 Oct 2026, 10:00 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Priceብር 400,00 (አራት መቶ ብር)
  • opening dateእሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም 4:30 ሰዓት
  • Categories Cleaning & Janitorial , Cleaning And Janitorial Equipment , Services

ሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን የፅዳት ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች ላይ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡


ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

ጨረታ ቁጥር ሰሜ/አ/አ/ሪ/ግ/ጨ/011/2018

ሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን የፅዳት ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች ላይ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

የዕቃዉ አይነት የመዝጊያ ቀን እና ሰዓት የመከፈቻ ቀን እና ሰዓት የጨረታ ዋስትና መስከበሪያ
የፅዳት እቃዎች ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት እሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም 4:30 ሰዓት 30,000.00 (ሰላሳ ሺህ ብር)
  1. ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ የተጨ.እ.ታ፤ የግብር ከፋይ መ/ቁጥር እና ከገቢዎች ባለስልጣን ጽ/ቤት ጨረታ ላይ እንዲሳተፉ የሚል ማስረጃ ያለው በጨረታው መሳተፍ ይችላል፡፡
  2. ተጫራቾች የመንግስት ድርጅቶች በሚያወጡት ጨረታ ላይ ለመሳተፍ እንዲችሉ በግዥ ኤጀንሲ ድህረ-ገፅ ላይ የተመዘገቡ ስለመሆናቸው ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  3. በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ ከላይ የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች በማያያዝ መወዳደር የሚችሉ ሲሆን ዝርዝር ሁኔታው በጨረታ ሰነዱ ውስጥ ይገኛል፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 400,00 (አራት መቶ ብር) በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000149984384(EEU N/A/A/R CU CON FOR EL CON) በሚለው ገቢ በማድረግ እና የከፈሉበትን የባንክ ስሊፕ ይዞ በመምጣት መውሰድ ይችላሉ፡፡
  5. አድራሻ፡- ፒያሳ አቡጎጴጥሮስ ፊት ለፊት አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር-210 በሚገኘው ሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ሰፕላይ ቼይን ግዥ እና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ፡፡
  6. ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የንዘብ መጠን ከላይ በሠንጠረዥ ውስጥ በተገለፀው መሠረት ሆኖ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ሲፒኦ /CPO/ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Bid Bond) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  7. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በሰም በታሸፈ ኤንቬሎፕ በማድረግ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል በአንድ ላይ በማድረግ «ኦሪጅናል እና ኮፒ» በማለት በተለያየ ፖስታ በማሸግ እና ሁለቱን በአንድ ትልቅ ፖስታ በማድረግ ጨረታ ቁጥር ሰሜ/አ/አ/ሪ/ግ/ጨ/011/2018 የሚል ምልክት በማድረግ እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ከላይ በተራ ቁጥር 5 ላይ በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት የሚኖርባቸው ሲሆን ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
  8. ጨረታው ከላይ በተገለፀው መሠረት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  9. ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0984820007 መደወል ይችላሉ፡፡
  10. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

የሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን

✨ messages.ai_summary
North Addis Ababa Region seeks bids from qualified cleaning supply companies for the open procurement of cleaning items. Eligible bidders must hold a renewed trade license, VAT registration, tax ID, and proof of registration on the procurement agency website.
Save Tender