ኦሮሚያ ባንክ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በትውልድ ኢትዮጵያዊ ሆነው የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ባለአክሲዮኖች በባንክ ወይም በኢንሹራንስ ያላቸው የአክሲዮን ድርሻ እንዲመለስላቸው ባወጣው መመሪያ ቁጥር FIS/01/2016 መሠረት (7 አዲስ የወጣ እና ሌሎች በድጋሚ የወጣ 53፣ 93፣ 182 እና 188) ባለ አክሲዮኖችን ለቀው የወጡት 523 አክሲዮኖችን ከዚህ በታች በተዘረዘረው አኳኋን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ኦሮሚያ ባንክ
የአክሲዮን ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ (LOT-30)
- ኦሮሚያ ባንክ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በትውልድ ኢትዮጵያዊ ሆነው የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ባለአክሲዮኖች በባንክ ወይም በኢንሹራንስ ያላቸው የአክሲዮን ድርሻ እንዲመለስላቸው ባወጣው መመሪያ ቁጥር FIS/01/2016 መሠረት (7 አዲስ የወጣ እና ሌሎች በድጋሚ የወጣ 53፣ 93፣ 182 እና 188) ባለ አክሲዮኖችን ለቀው የወጡት 523 አክሲዮኖችን ከዚህ በታች በተዘረዘረው አኳኋን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። የአንድ አክሲዮን የጨረታ መነሻ ዋጋ ብር 1,000.00 (አንድ ሺህ ብር) ሲሆን፤ ለጨረታው የቀረበው ብዛት 7፣ 53፣ 93፣ 182 እና 188 አክሲዮን ነው።
- ተጫራቾች መግዛት የሚችሉት አነስተኛ የአክስዮን ብዛት 7፣ 53፣ 93፣ 182 እና 188 ሲሆን ከዚህ ውጪ የሆኑ አክሲዮኖችን ለመግዛት የሚቀርብ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረውም።
- ተጫራቾች መጫረት የሚፈልጉትን የአክሲዮን ብዛት ጠቅላላ መነሻ ዋጋ 2% የጨረታ ማስከበሪያ ቦንድ በባንክ ክፍያ ማዘዣ ሲፒኦ አሰርተው እና ለዚህ ዓላማ የተዘጋጀውን ቅጽ ሞልተው አንድ ላይ በማያያዝ ከጨረታው ቀን በፊት የፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት 9ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 9-004 በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ሕዳር 08 ቀን 2018 ዓ.ም 8:00 ሰዓት ተዘግቶ ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸውና ታዛቢዎች በተገኙበት፣ ቦሌ ደንበል፣ ጌቱ ኮሜርሻል አጠገብ (ቦሌ ሸዋ ዳቦ ፊት ለፊት) በሚገኘው የኦሮሚያ ባንክ 9ኛ ፎቅ ዋናው መ/ቤት ውስጥ ይከፈታል።
- በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ዋጋ በአምስት (5) ቀናት ውስጥ ለባንኩ ገቢ ማድረግ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሆነው የውጭ ዜግነት ያላቸው ከሆነ ጨረታውን ካሸነፉ ያሸነፉበትን ዋጋ የሚከፍሉት ከውጪ ምንዛሪ አካውንት (ዲያስፖራ አካውንት) እና ለዚሁም በቂ ማስረጃ የሚያቀርቡ መሆን አለባቸው። እንዲሁም ድርጅቶች ከሆኑ የድርጅቱ ባለአክሲዮኖች በሙሉ ኢትዮጵያዊ በሆኑ ዜጎች የተያዙ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ በቂ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ተጫራቾች የማስረጃቸውን ፎቶ ኮፒ ከሚሞሉት ቅፅ ጋር አያይዘው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-557-20-80/82/011-558-83-21 ዋናው መ/ቤት ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
- ተጫራቾች ሌሎች ባቀረቡት ዋጋ ላይ ተንተርሰው ዋጋ ማቅረብ አይችሉም።
- ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
