Tender Detail

Tender Details

  • Company በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን መ/ቤት
  • Address ኮምቦልቻ ከተማ ፡ አማራ ክልል ፡ ኢትዯጵያ, Phone: 033 351 33 37
  • Website
  • Deadline14 Nov 2024, 10:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date
  • Categories Vehicle tire

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን መ/ቤት በ2017 በጀት አመት ከመደበኛ እና ካፒታል በጀት ለመ/ቤቱ የተለያዩ ተሽከርካሪዎችና ማሸነሪዎች አገልግሎት የሚውል መለዋወጫ (ስፔር ፓርት) በሎት 1/አንድ/ እንዲሁም ጎማና ባትሪ በሎት 2/ሁለት/ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል::


የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን /ቤት 2017 በጀት አመት ከመደበኛ እና ካፒታል በጀት ለመ/ቤቱ የተለያዩ ተሽከርካሪዎችና ማሸነሪዎች አገልግሎት የሚውል መለዋወጫ (ስፔር ፓርት) በሎት 1/አንድ/ እንዲሁም ጎማና ባትሪ በሎት 2/ሁለት/ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል::

በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት የምትችሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

  1. በዘመኑና በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ስራ ፈቃድ ያለው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN NO) ያላቸዉ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፡፡
  3. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-2 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸዉ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. ጨረታው ጸንቶ የሚቆይበት ጊዜ የጨረታ ሰነዱ ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ 60 ቀናት ሲሆን ተጫራቾች የጨረታ ማሰከበሪያ ዋስትና (BID BOND) ብር የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 2% በማስላት በባንከ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ (CPO) በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ለእያንዳንዱ ሎት ለየብቻ በማሰራት ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ ማቅረብ አለበት፡፡
  5. ማንኛውም ተጫራች /ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሰነድ በሚጠይቀው የዋጋ አሞላል ብቻ መሙላት አለበት:: በሚጠይቀው ዋጋ አሞላል ካልሞሉ የጨረታ ሰነዱ ውድቅ ይሆናል።
  6. የጨረታው ውድድር የሚካሄደው በሎት /በጥቅል/ ድምር ውጤት ስለሆነ የማይሞላ አይተም መኖር የለበትም ያልተሞላ አይተም ከተገኘ ከጨረታው ውድቅ ይሆናሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ዝረዝር መግለጫ (ስፔስፊኪሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 400.00 (አራት መቶ ብር) በመክፈል ከግ/ ፋይ//አስ//የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  9. ጨረታው አየር ላይ የሚቆየው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 20/02/2017 / እስከ 4/3/2017 / 1130 ድረስ መግዛት ይችላሉ፡፡
  10. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ አንድ ቅጅ ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት ለየብቻ በጥንቃቄ በታሸገ ፖሰታ መንገዶች ባለስልጣን /ቤት በግዥና/ፋይ//አስ//የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ 5/3/2017 / ቀን 400 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  11. ጨረታዉ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በግዥና ፋይ// አስ//የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 5/3/2017 / 400 ሰዓት ታሽጎ 430 ላይ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜ እሁድና የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት መሆኑን እንገልጻልን፡፡
  12. /ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰርዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. ለበለጠ መረጃ በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን /ቤት በአካል በመቅረብ ወይንም በስልክ ቁጥር 033 351 33 37/033 551 05 04/ መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ማሳሰቢያ፡- የመስሪያ ቤቱ አድራሻ ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ህንጻ አምስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 508 ላይ ነው፡፡

 

አማራ  ብሄራዊ  ክልላዊ  መንግስት  የኮምቦልቻ  ከተማ  አስተዳደር

መንገዶች ባለስልጣን  /ቤት

Save Tender