የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ በ2017 የበጀት ዓ.ም ለሰልጣኞች አገልግሎት የሚውል የተለያዩ የቢሮ እቃዎች፤ የኤሌከትሮኒክስ እቃዎች፣ የመኪና መለዋወጫ እቃዎች፣ የውሃ ዕቃዎች የመብራት ዕቃዎች፤ የተለያዩ የግንባታ ጥገና እቃዎች፣ የቢሮ የቢሮ እና የስብሰባ አዳራሽ ወንበሮች እና የተለያዩ አይነት አልባሳትን ማለትም የእስፓርት ልብስ ቱታ ቶርሽን ጫማ፤ ቁምጣ እና ቲሸርት፤ የጀርባ ቦርሳ፤ ትልቁ ፎጣ የሻወር፤ መካከለኛ ፎጣ የራስ የእስፖርት ኮፊያ፤ ፊሽካ ለቶርሽን ጫማ የሚሆን ካልሲ እና ጥቁር ካልሲ ወፍራም ለከስክስ ፎጣ የሚሆን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የግዥ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ 2/2017
የጨረታ ቁጥር ኦፖኮ/02/2017
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ በ2017 የበጀት ዓ.ም ለሰልጣኞች አገልግሎት የሚውል የተለያዩ የቢሮ እቃዎች፤ የኤሌከትሮኒክስ እቃዎች፣ የመኪና መለዋወጫ እቃዎች፣ የውሃ ዕቃዎች የመብራት ዕቃዎች፤ የተለያዩ የግንባታ ጥገና እቃዎች፣ የቢሮ የቢሮ እና የስብሰባ አዳራሽ ወንበሮች እና የተለያዩ አይነት አልባሳትን ማለትም የእስፓርት ልብስ ቱታ ቶርሽን ጫማ፤ ቁምጣ እና ቲሸርት፤ የጀርባ ቦርሳ፤ ትልቁ ፎጣ የሻወር፤ መካከለኛ ፎጣ የራስ የእስፖርት ኮፊያ፤ ፊሽካ ለቶርሽን ጫማ የሚሆን ካልሲ እና ጥቁር ካልሲ ወፍራም ለከስክስ ፎጣ የሚሆን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። በዚህ መሰረት በጨረታው ለመሳተፍ ለምትፈልጉ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው ተጫራቾች የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ አዳማ የጨረታውን ሰነድ በመግዛት ጨረታው ላይ መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ለመወዳደር የምትፈልጉ ድርጅቶች፤ ነጋዴዎች አቅራቢዎች ፤-
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ የ2016/2017 ያለውና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፤
- የሥራ ግብር ከፋይ መሆኑን የሚገልፅ የቲን ቁጥር መረጃ ማቅረብ የሚችል
- ተጫራቾእ በአቅራቢዎች ስም ዝርዝር (Supply List) ውስጥ መመዝገባቸውን የሚገልፅ መረጃ ማቅረብ የሚችል።
- ግብር መከፈላቸውን የሚገልፅ መረጃ (ክሊራንስ) ማቅረብ የሚችል፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT 15%) ተመዝጋቢ መሆኑን የሚገልፅ መረጃ ማቅረብ የሚችል።
- ማንኛውም ተጫራች ለውድድር ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ የጨረታ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ (CPO) 2% ከጨረታ ሰነድ ጋር በፖስታ አሽጎ ማቅረብ አለባቸው።
- የጨረታ ሰነዱ የተዘጋጀው በኦሮሚኛ ቋንቋ ስለሆነ ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ማስታወቂያው ከወጣበትን ቀን ጀምሮ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ የጨረታ ሰነዱን በኮሌጅ ቅጥር ግቢ ፋይናንስ ቢሮ በማቅረብ መውሰድ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናውንና ኮፒውን በተናጥል በፖስታ አሽገው ማቅረብ አለባቸው::
- የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እሁድን ሳይጨምር ለ15 (አስራ አምስት ተከታታይ ቀናት ክፍት ሆኖ ቆይቶ በ16ኛው ቀን እስከ 6፡00 ሰዓት ተሸጦ የጨረታው ሰነድ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ገብቶ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 6፡30 ሰዓት ላይ ታሽጎ በዚሁ ቀን ከሰዓት በኋላ በ8፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በይፋ በኮሌጁ አዳራሽ ውስጥ ይከፈታል፡፡
- ኮሌጁ በሚገዛው ማንኛውም ዕቃ ላይ 50% የመቀነስና የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ኮሌጁ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- አጠቃላይ ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነድ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስ/ቁጥር 0942410695 0913379464 አና 0941734430 ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ።
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ
