የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2017 በጀት አመት ለሴክተር መስሪያ ቤቶች የሚሆን የመኪና ጎማ በግልጽ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ።
የጨረታ ማስታወቂያ
የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2017 በጀት አመት ለሴክተር መስሪያ ቤቶች የሚሆን የመኪና ጎማ በግልጽ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ።
በመሆኑም ፤
- የዘመኑን የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችል
- የአቅራቢነት ምዝገባ ሠርተፊኬት ማቅረብ የሚችል
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5,000 (አምስት ሺ) በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ ጋራንቲ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ሰነዱን ከስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በመቅረብ የማይመለስ 100 (መቶ) ብር ብቻ በመክፈል መግዛት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ሰነዱን በሚገባ በመሙላት አንድ ኦርጂናልና 1 ኮፒ ለየብቻ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፤ የጨረታ ሳጥኑ በ15ኛው ቀን በ8፡00 ሰዓት ታሽጎ 8፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 5ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
መምሪያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው :
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0467710016/082/083
የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
