በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪከት ልዩ ልዩ መጠን ያላቸው ያገለገሉ ጐማዎችን በግልፅ ጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 005/2017
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪከት ልዩ ልዩ መጠን ያላቸው ያገለገሉ ጐማዎችን በግልፅ ጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፊኬት (Tin Number) ያለው እንዲሁም የዘመኑን ግብር የከፈሉበት መረጃ እና የታደሰ መታወቂያ በማቅረብ የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታው አሸናፊ የሚወሰነው በጨረታው ሰነድ ውስጥ የተመለከቱትን መስፈርቶች አሟልቶ ከፍተኛ ዋጋ የሚያቀርብ ነው::
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን አሟልቶ በታሸገ ፖስታ በማድረግ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት የሚችለው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ብቻ ነው::
- ተጫራቾች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች ሁሉንም የመጫረት ግዴታ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 15,000 (አስራ አምስት ሺ ብር) በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ስም አሠርተው በባንክ የተረጋገጠ (CPO) ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ በ4፡30 ሰዓት ኮምቦልቻ በሚገኘው በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ቅጥር ግቢ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር ፡- 033 551 02 05/ 033 551 30 02/ 033 551 22 68 ማግኘት ይችላሉ::
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት
