የሀዋሳ ከተማ መ/ው/ፍ/አገ ድርጅት የመኪና እና የሞተር ሳይክል ጎማ በግልጽ ጨረታ አወዳደሮ ግዥ ለመፈጸም ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የመኪና እና የሞተር ሣይክል ጎማ
የግዥ መለያ ቁጥር ግ/ጎማ/01/2017
የሀዋሳ ከተማ መ/ው/ፍ/አገ ድርጅት የመኪና እና የሞተር ሳይክል ጎማ በግልጽ ጨረታ አወዳደሮ ግዥ ለመፈጸም ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልግ ድርጅት ከዚህ በታች በሠንጠረዥ በተገለጸው ዝርዝር መሠረት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ፡፡
|
ሎት |
መግለጫ |
መለኪያ |
ብዛት |
|
ሎት 1 |
የተለየዩ መጠን ያላቸውን የትልቁ እና ትንሹ መኪና ጎማ እና ከመነዳሪ |
በቁጥር |
67 |
|
ሎት 2 |
የተለያዩ መጠን ያላቸውን የሞተር ሳይክል ጎማ እና ከነመዳሪ |
በቁጥር |
184 |
በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ፡-
- ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው የ2016 ዓ.ም የዘመኑን ግብር የተከፈለበት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለው እና የተጨማሪ እሴት ታከስ /ቫት ተመዝጋቢ የሆነ፡፡
- የጨረታ ዋስትና መያዣ ብር 50000 /ሃምሳ ሺህ ብር ብቻ/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ግዥውን በሚፈጽመው ድርጅት ስም ተዘጋጅቶ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ እንዲሁም ከተጠየቀው ሲፒኦ ማስያዣ ውጪ የቀረበ ማስያዣ ጨረታው ሳይከፈት ውድቅ ይደረጋል፡፡
- የተዘጋጀውን የመኪና እና የሞተር ሳይክል ጎማ መጠንና ዓይነትና ዝርዝር መረጃ የሚገልጽ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 800 /ስምንት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ከሀዋሳ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የግዥ/አስ/ቡድን መሪ ቢሮ ቁጥር 19 ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ዶክመንቱን ለመግዛት ሲመጡ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ኮፒ ይዞ መምጣት አለበት፡፡
- ተጫራቾች በሰነዶቻቸው ላይ ስማቸውን ሙሉ አድራሻቸውን ፊርማቸውን አሟልተው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ዋናውን እና 2 /ሁለት/ ኮፒ ለየብቻ በማድረግ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ ሰነዶችን ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ20 ተከታታይ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት እስከ 11፡00 ሰዓት ድረስ ከሃዋሳ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ግዥ አስተዳደር ቡድን መሪ ቢሮ ቁጥር 19 በመምጣት የተዘጋጀውን የጨረታ ዶክመንት መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች በ21ኛው ቀን የጨረታ ዶክመንታቸውን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 8፡00 ሰዓት ድረስ ድርጅቱ ለጨረታ ባዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡ ጨረታው የሚከፈተው በ21ኛው ቀን በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ሆኖም 21ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር፡- 046 212 1580/046 22191 12
አድራሻ ፡- ከወልደአማኑኤል አደባባይ በግራ በኩል ወደ አዲሱ መናኸሪያ በሚወስደው መንገድ 200 ሜትር አስፋልት ፊት ለፊት
የሀዋሳ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት
