በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጉለሌ ክ/ከተማ የወረዳ 3 ት/ጽ/ቤት የፀሐይ ጮራ ቅ/አንደኛ አ/መ/ደ/ት/ቤት ለ2017 ዓ/ም በመደበኛ በጀት
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ መለያ ቁጥር 003/2017
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጉለሌ ክ/ከተማ የወረዳ 3 ት/ጽ/ቤት የፀሐይ ጮራ ቅ/አንደኛ አ/መ/ደ/ት/ቤት ለ2017 ዓ/ም በመደበኛ በጀት
የደንብ ልብስ እና የደንብ ልብስ ማሰፊያ
- ሎት 2፡-አላቂ የቢሮ እቃዎች ፣
- ሎት 3፡- ህትመት
- ሎት4:- አላቂ የህክምና እቃዎች
- ሎት5፦ አላቂ የትምህርት እቃዎች
- ሎት 6፡- ሌሎች አላቂ እቃዎች
- ሎት 7፣ ማሽነሪ መሣሪያ ጥገና
- ሎት 8፡ አጠቃላይ ጥገና
- ሎት 9፡ ቋሚ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፡-
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ አግባብነት ያለው የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለው
- በመንግሥት ግዥ ኤጀንሲ በእቃ አቅራቢነት የተመዘገበ ኮፒ ማቅረብ የሚችል
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ስለመመዝገባቸው የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት የማይመለሰ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ሰነዱን ከግዥ ከፍል መውሰድ ይችላሉ ፡፡
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በገዙት ሰነድ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ ቦታ በመግለጽ መሙላት አለባቸው
- ተጫራቾች የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ ብር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተፈቀደላቸው የታወቁ ባንኮች የሚሰጥ ሆኖ በተረጋገጠ ክፍያ ሲፒኦ (cpo) ማስያዝ አለባቸው፡፡ ሎት1፡-የደንብ ልብስ እና የደንብ ልብስ ማሰፊያ፡- 9763 ሎት 2፡-አላቂ የቢሮ እቃዎች፡-234.80 ሎት3፡-ሕትመት-80 ሎት 4፡- አላቂ የሕክምና እቃዎች-200.00 ሎት 5፡- አላቂ የትምሕርት እቃዎች 6.709 ሎት 6፡ ሌሎች አላቂ እቃዎች 1,940 ሎት7፣ ማሽነሪ መሣሪያ ጥገና፡ሎት 8፡ አጠቃላይ የጥገና -399.75 ሎት 9፡ ቋሚ እቃዎች 6,433 ናሙና ለሚያስፈልጋቸው እቃዎች ጨረታው ከመዘጋቱ በፊትማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ናሙና ያላቀረቡ ተጫራቾች ከጨረታው ይሰረዛሉ፤ ናሙና ለማይቀርብላቸው እቃዎች በቀረበው የዕቃ መግለጫ (specification) መሰረት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- አነስተኛ እና ጥቃቅን እቃ አቅራቢዎች ከሚመለከተው አካል በትምሕርት ቤቱ ስም የተፃፈ አምራች መሆናቸውን የሚገልጽ ዋስትናውን የሚወስድ ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናውንና ኮፒ በታሸገ ኤንቨሎፕ በግዥ ከፍል በሚገኘው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል ፡፡
- ጨረታው ማስታወቂያ ከወጣበት በ10ኛው የሥራ ቀን ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ11ኛው ቀን በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ፋይናንስ ቢሮ 19 ይከፈታል፡፡ ዕለቱ በዓል ወይም ዝግ ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተገለፀው ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ሲያሸንፉ ከአሸነፋበት ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- በጨረታ አሸናፊው ድርጅት ውል ከፈረሙበት ቀን ጀምሮ ባሉት በ10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን እቃ ማንኛውንም የትራንስፖርት ወጭ በራሳቸው ትራንስፖርት ት/ቤቱ ንብረት ክፍል ገቢ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡
- ት/ቤቱ እንደ አስፈላጊነቱ ከውል በፊት የእቃው ብዛት 20% የመጨመር ወይም 20% የመቀነስ መብት አለው፡፡
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- 5 ኪሎ ከመነን ት/ቤት ከፍ ብሎ ወደ ሽሮ ሜዳ በሚወስደው መንገድ ከወረዳ 3
አስተዳደር ጽ/ቤት ፊት ለፊት ይገኛል፡፡
ስልክ ቁጥር፡ 011-126-09-75 ወይም 011-126 85 011-126-8508/011 268794
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጉለሌ ከ/ከተማ የወረዳ 3 ት/ጽ/ቤት የፀሐይ ጮራ ቅ/አ/አ/መ/ደ/ት/ቤት
