የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት በድርጅቱ መጋዘኖች ውስጥ ተከማችቶ የሚገኘውን የበቆሎ፣ የስንዴ፣ የቦሎቄ ተረፈ ምርቶችንና ያገለገሉ ባለ 100 ኪ.ግ ፖሊባጎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡- 003/ሽያጭ/17 ዓ.ም
የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት በድርጅቱ መጋዘኖች ውስጥ ተከማችቶ የሚገኘውን የበቆሎ፣ የስንዴ፣ የቦሎቄ ተረፈ ምርቶችንና ያገለገሉ ባለ 100 ኪ.ግ ፖሊባጎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
በዚሁም መሠረት ፡-
-
- ተጫራቶች በሥራ ዘርፉ የተሰማሩና የታደሰ ህጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN)፤ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ብር 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/ ብቻ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሰከረለት የክፍያ ማዘዣ (CPO) በደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት ስም ከጨረታ ኦሪጅናል ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ድረስ በሥራ ሰዓት የማይመለስ ብር 300 በመክፈል ናሙና አይቶ በሀዋሣ ከተማ በሚገኘው በድርጅቱ የግዥ ፋይ/ንብ/አስተዳደር ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በሰም /በማይለቅ/ በታሸገ ፖስታ /ኤንቨሎፕ/ ውስጥ በማድረግ ኦሪጂናልና ኮፒውን ከተጓዳኝ ማስረጃዎች ጋር በማደራጀት በድርጅቱ የግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በመቅረብ ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ በ15ኛው ቀን እስከ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት አለባቸው::
- የጨረታው ሳጥን የጨረታ ማስታወቂያው በወጣ በ15ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ በ8፡30 ሰዓት በድርጅቱ የግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ነገር ግን 15ኛው ቀን የሥራ ቀን ባይሆን በቀጣዩ የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ተመሳሳይ ቦታ ሰዓትና ሁኔታ ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነዶቻቸው ላይ ሙሉ ስማቸውን፤ ፊርማቸውን እና የድርጅታቸውን ማህተም ማድረግ አለባቸው::
- ድርጅቱ ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር፡- 046-2-20-59-92/ 09-16-83-66-53
የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት
