በኮ/ቀ/ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የረጲ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ2017 ዓ.ም የስራ ዘመን ከዚህ በታች በሎት የተደራጁ እቃዎችን በ2ኛ ዙር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በኮ/ቀ/ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የረጲ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ2017 ዓ.ም የስራ ዘመን ከዚህ በታች በሎት የተደራጁ እቃዎችን በ2ኛ ዙር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
- ሎት 1. የፅዳት እቃዎች፣ ሎት 2- የደንብ ልብስ፣ ሎት 3. የቢሮ መገልገያ ቋሚ እቃዎችና ኤሌክትሮኒከስ እቃዎች ሎት 4- የተለያዩ ጥገናዎች (የውሃ መስመር እና የጄነሬተር ጥገና ስራ) በመሆኑም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ለእያንዳንዱ ሎት በመክፈል በኮ/ቀ/ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የረጲ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ኮ/ቀ/ክ/ ከተማ ወረዳ 02 አለፍ ብሎ ካራቆሬ አጃንባ መውጫ አካባቢ ቢሮ ቁጥር 71 ቀርበው መውሰድ እንደሚችሉ እናሳውቃለን፡፡
- ተጫራቾች የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ እና የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የግብር ከፋይነት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ተመዝጋቢዎች መሆን አለባቸው::
- የሚቀርበው የዋጋ ሰነድ ቫትን ያካተተ መሆን አለበት፡፡
- ጨረታ ላይ እንዲሳተፉ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ከገቢዎች ጊዜው ያላለፈ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
- የአቅራቢነት ምዝገባ በኦላይን የተመዘገበ መሆን አለበት፡፡
- በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጃቹ ተጫራቾች ደብዳቤው ባደራጃቹ ሃላፊ የተፈረመ እና አምራች ድርጅት መሆናቹ የሚገልጽ መሆን አለበት፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው ሲከፈት የጨረታ ማስከበሪያ
ሎት 1. 10,000.00 /አስር ሺ ብር/
ሎት 2. 4,363.00 /አራት ሺ ሶስት መቶ ስልሳ ሶስት ብር/
ሎት 3. 7,000.00 /ሰባት ሺ ብር/
ሎት 4. 3,000.00 /ሶስት ሺ ብር ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- አሸናፊው ተጫራች በሰነዱ ውስጥ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ ቀርቦ ውል መዋዋል አለባቸው።
- ማንኛውም ተጫራች የሚያቀርበውን ሰነድ ዋናውን እና ፎቶ ኮፒውን ለየብቻ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባት ይችላሉ።
- አሸናፊ ድርጅት ያሸነፉበትን እቃ 10% ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለሚያቀርቡት እቃ ናሙና ማቅረብ አለባቸው፤ ናሙና ያላቀረበ ድርጅት ከውድድር ውጪ ይሆናል፡፡ እቃው በናሙናው ላይ ያለውን የጥራት ደረጃ ይዞ ካልተገኘ ተመላሽ ይደረጋል፡፡
- ገዢው በአካል የሚገዛውን እቃ እስከ 20% ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል፡፡
- ለአሸናፊ ተጫራቾች በሰነድ ውስጥ የተካተተውን ጊዜ ገደብ ውስጥ ማለትም እስከ 10 ቀን ድረስ ቀርበው የውል ማስከበሪያ ሲፒኦ አሰርተው ውል መዋዋል አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ተወዳድረው ያሸነፉባቸውን እቃዎች በወቅቱ ማቅረብ ካልቻሉ ያስያዙት ሲፒኦ ይወረሳል /ተመላሽ አይደረግም፡፡
- የእቃ ማስረከቢያ ቦታ ረጲ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ይሆናል፡፡
- በሚቀርበው የጨረታ ሰነድ ላይ የድርጅቱ ሀላፊ ስምና ፊርማ የድርጅቱ አድራሻ እና ስልክ ቁጥር መኖር አለበት፡፡
- ት/ቤቱ ተገቢ ነው ብሎ ካመነበት ከጨረታው አሸናፊ ድርጅት ጋር እስከ 6 ወር ድረስ ውሉን ባያድስም የመግዛት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ከወጣበት የመጀመሪያው ቀን አንስቶ ለሚቆጠር 10 ተከታታይ ቀናት ቅዳሜና እሁድ ጨምሮ ክፍት ሆኖ ይቆይና በ11ኛው ቀን ጠዋት 3፡00 ሰዓት ታሽጎ 3፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በረጲ 2ኛ ደ/ት/ቤት በሂሳብ ክፍል ቢሮ ቁጥር 71 ውስጥ ይከፈታል፡፡
- የዕቃ ማጓጓዣ ብር አሸናፊው ተጫራች ይሸፍናል፡፡
- ት/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ ፡- በኮ/ቀ/ክ/ከ ወረዳ 11 የረጲ 2ኛ ደ/ት/ቤት ፋይናንስ ቢሮ ውስጥ ሲሆን
ለበለጠ መረጃ ስልክ :- 0113 48 8850, 0113 47 18 16 እና 0113694156
የረጲ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
