Tender Detail

Tender Details


በአዲስ አበባ ከተማ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ በ2017 በጀት አመት ከዚህ በታች በተለያዬ በምድብ (ሎት) የተከፋፈሉትን ዕቃዎች እና ተያያዥ አገልግሎቶች በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳደሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል፡፡


 

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር ግመ007/2017

 

በአዲስ አበባ ከተማ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ 2017 በጀት አመት ከዚህ በታች በተለያዬ በምድብ (ሎት) የተከፋፈሉትን ዕቃዎች እና ተያያዥ አገልግሎቶች በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳደሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት፡-

 

ምድብ (ሎት)

የዕቃው/አገልግሎት አይነት

የጨረታ ሰነድ መሸጫ ዋጋ

የጨረታ ማስከበሪያ

ምድብ 001

ለረጲ ደረቅ ቆሻሻ ማስወገድ አገልግሎት የሚውል ዶዘር ማሽን ኪራይ

ብር 300.00

80,000.00 ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒአ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ባንክ ጋራንቲ

ምድብ 002

ገረጋንቲና ቦልድ ድንጋይ

ብር 300.00

150,000.00 ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒአ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ባንክ ጋራንቲ

ምድብ 003

ለጋዝ ማስተንፈሻ አገልግሎት የሚውሉ የግንባታ ዕቃዎች

ብር 300.00

20,000.00 ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ባንክ ጋራንቲ

ምድብ 004

የዲጂታል ማስታወቂያ ቦርድ (ዲጂታል ሳይንኤጂ)

ብር 300.00

20,000.00 ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒአ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ባንክ ጋራንቲ

ምድብ 005

ሞንታርቦ ከእነአከሰሰሪው

ብር 300.00

20,000.00 ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ባንክ ጋራንቲ

ምድብ 006

መንገድ ዳር የሚተከል ደስት ቢን

ብር 300.00

60,000.00 ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ባንከ ጋራንቲ

ምድብ 007

የተለያዩ የቢሮ ዕቃዎች

ብር 300.00

30,000.00 ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ባንክ ጋራንቲ

ምድብ 008

የቀላል ተሽከርካሪ ጎማዎች እና አላቂ ዕቃዎች

ብር 300.00

15,000.00 ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ባንክ ጋራንቲ

 

ከዚህ በታች የተጠቀሱትን ዝርዝር መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በጨረታው መሳተፍ ትችላላችሁ፡፡

  1. በዘርፉ ሕጋዊና የታደሰ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችል፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው፣ ከዕዳ ነጻ ስለመሆናቸው ክሊራንስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፤ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ (VAT (15%)) ተመዝጋቢ የሆነ፣ በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገበ፣
  2. ጨረታውን ያሸነፈው ድርጅት ማሸነፉ እንደተገለፀለት የውል ማስከበሪያ የውሉን ጠቅላላ ዋጋ 10 (አስር) በመቶ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚሰራና ሕጋዊ ዕውቅና ካለው ተቋም .. በማቅረብ 15 ቀናት ውስጥ ቀርቦ ውል መፈፀም የሚችል፣
  3. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያ (ፋይናንሻል ሰነድ) ኦርጅናልና ኮፒ፤ ቴክኒካል ሰነድ ኦርጅናልና ኮፒ ብሎ በመለዬት ለየብቻው በጥንቃቄ በፖስታ በማሸግ የድርጅቱን ሕጋዊ ማኅተምና ፊርማ በማድረግ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ የመንግስት ግዥ ዳይሬክተር ቢሮ 10 ወለል በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፣
  4. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ዘወትር በሥራ ሰአት (ቅዳሜና እሑድን ሳይጨምር) በአዲስ አበባ ከተማ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ 9 ወለል በመገኘት የጨረታ ሰነዱን በብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፣
  5. ጨረታው የሚከፈትበት ዕለት የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አየር ላይ ከዋለ 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት በኋላ 11ኛው ቀን ጠዋት 400 ሰዓት ላይ ጨረታው ተዘግቶ በዚሁ ዕለት 430 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ነገርግን ጨረታው የሚከፈትበት ዕለት ሕዝባዊ ወይም ኃይማኖታዊ በዓል ከሆነ ወይም ቅዳሜና እሑድ ከሆነ ሌላ ማስታወቂያ ማውጣት ሳያስፈልግ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተጠቀሰው ቦታና ሰዓት ይከፈታል፣ በምድብ 006 ምድብ 007 እና ምድብ 008 የተጠቀሱ ግዥዎች ቅድሚያ ናሙና/ሳምፕል/ ማቅረብ የሚችል፡፡
  6. ተጫራቾች በጨረታው አከፋፈት ስርዓት ላይ በራሳቸው ፈቃድ ባይገኙ ጨረታው አይስተጓጎልም፣
  7. ኤጀንሲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

አድራሻ፡- በአዲስ አበባ ከተማ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ፒያሳ በተለምዶ እሪ በከንቱ ተብሎ በሚጠራው 15 ቀበሌ ኢትዮ ሴራሚክስ ጎን (ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ፊት ለፊት ከሚገኘው ቢቲ ታዎር (ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር ከሚገኝበት ሕንጻ) የመንግስት ግዥ ዳይሬክተር 10 ወለል ነው፡፡ ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር፡- 011 275 0002 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

 

በአዲስ አበባ /አስተዳደር የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ

Save Tender