በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በከተማው መስተዳድር ስር ለሚግኙ ሴክተር መ/ቤቶች ለተለያዩ የሰራተኞች የደንብ ልብሶችን እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች የሚውሉ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በከተማው መስተዳድር ስር ለሚግኙ ሴክተር መ/ቤቶች ለተለያዩ የሰራተኞች የደንብ ልብሶችን እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች የሚውሉ መግዛት ይፈልጋል።
- የሰራተኛ የደንብ ልብሶች
- የኤሌክትሮኒክስ እና የአዳራሽ ውስጥ እስክሪን እቃዎች
በዘርፉ ከተሰማሩ አቅራቢዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ :-
- ተጫራቾች በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉና የዘመኑን ግብር ከፍለው ማጠናቀቃቸውንና ጨረታ ላይ እንዲሳተፉ የሚል ማስረጃ ከሀገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣን ጽ/ቤት ማቅረብ አለባቸው።
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋገጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በጽ/ቤቱ ስም ሲፒኦ ባንክ በሂሳብ ቂጥር 1054551161211 ላይ ገቢ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት እለት ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት በጽ/ቤቱ የግዢ የስራ ሂደት ቢሮ ድረስ በመቅረብ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TN No.) የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡና የምስክር ወረቀት ያላቸው::
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የተጠቀሰውን ማስረጃዎች ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻችው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ከአዳማ ከተማ ገንዘብ ጽ/ቤት በሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለሚያቀርቡት የጨረታ ዋጋ ለእያንዳንዱ ማስከበሪያ CPO ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) ሲሆን በጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ለተደራጁ የትኛውንም የዋስትና ደብዳቤ የማንቀበል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
- ተጫራቾች ሰነዳቸውን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ኮፒና ኦረጅናሉን ለየብቻው ታሽጎ መቅረብ አለበት። ቴክኒካሉን ያልፉት ተወዳዳሪዎች ፋይናንሻላቸው ይከፈታል።
- ጨረታው የሚከፈተው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት በ 16ኛው ቀን የስራ ቀን ከሆነ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ8:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በአዳማ ከተማ ገንዘብ/ፅ/ቤት ሶስተኛ ፎቅ ገዢ ክፍል ውስጥ ይከፈታል፡፡ እለቱ በዓል ወይም መ/ቤቱ ዝግ ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን በተጠቀሰው ሰዓት ጨረታው ይከፈታል፡፡
- ማንኛውም የደንብ ልብስ ተወዳዳሪዎች ሳምፕል ወይም ናሙና ማቅረብ አለባቸው::
- የጨረታው አሸናፊ ዕቃዎቹን እስከ አዳማ ከተማ ገንዘብ ጽ/ቤት መጋዘን ድረስ በራሳቸው ወጪ አጓጉዘው ማቅረብ አለባቸው::
- የጨረታ አሸናፊ በጨረታ መመሪያ በተሰጠው መሰረት የጨረታ አሸናፊነቱ በውስጥ ማስታውቂያ እና በስልክ እንደተገለፀ በ10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ አስፈላጊውን የጨረታ ውል ከአዳማ ከተማ ገንዘብ ፅ/ቤት ጋር መፈራረም አለበት፡፡ ይህ ባይፈፀም የጨረታ አሸናፊነቱን በመሰረዝ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ገቢ ይሆናል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ለውድድር የሚቀርበው ቫት ተጠቃሚ ሲሆን ፣ 7.5 % በክፍያ ጊዜ የሚቀነስ ይሆናል።
- መስሪያ ቤቱ ከሚያደርገው የግዢው 20 ፐርሰንት መጨመር ወይም መቀነስ የሚችል መሆኑን ተጫራቹ መገንዘብ አለበት፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፈልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 022-2-11-14-42 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት
