የአ/ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ለሠራተኞች የድንብ ልብስ የጨርቅ አቅርቦት ከድርጅቱ ሆና የስፌት ሥራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለሰራተኞች ጨርቁን ለማሠፋት ይፈልጋል ፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የአ/ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ለሠራተኞች የድንብ ልብስ የጨርቅ አቅርቦት ከድርጅቱ ሆና የስፌት ሥራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለሰራተኞች ጨርቁን ለማሠፋት ይፈልጋል ፡፡ በዚህም መሰረት
1ኛ. የደንበል ልብስ የስፌት ሥራ
2ኛ. ከላይ በተራ ቁጥር አንድ በተጠቀሰው የሥራ ዘርፍ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለውና የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈለ እንዲሁም በዘርፉ በቀጥታ ተሳታፊ መሆኑን የሚገልፅ ማስረጃ ያለው
3ኛ በዘርፉ የታደሰ ፈቃድ ያለው፣ የተጨማሪ እሴት ታክሰ ተመዝጋቢ መሆናቸውንና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /TIN/ መኖሩን የሚገልጽ ማስረጃ እና ሌሎችን መረጃዎች አሟልቶ ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት፡፡
4ኛ. ተጫራቾች በጨረታው ሠነድ ላይ የተዘረዘሩትን የልብስ ዓይነት በትክክል አይተው የስፌት ዋጋውን መሙላት አለባቸው
5ኛ. ተወዳድሮ ሲያሸንፍ ወዲያውኑ ከድርጅቱ ጋር ውል ገብቶ የስፌት ሥራ መሥራት የሚችል መሆን አለበት።
6ኛ. ተጫራቹ ጨረታውን ሲያሸንፉ ወዲያውኑ የስፌት ማሽን ወደ ድርጅቱ ጊቢ በማቅረብ በሠራተኞች ልክ የታዘዘላቸውን የልብስ ዓይነት መስፋት የሚችል መሆን አለባቸው::
7ኛ. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው ከታወቁ ባንኮች ብር 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ cpo ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ከጨረታ ዶክመንት ጋር ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
8ኛ. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ከፍሎ ከድርጅቱ በመውሰድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ/ፖስታ ቴክኒካል ዶክመንት ኦርጅናል ለብቻ ቴክኒካል ዶክመንት ኮፒ ለብቻ እንዲሁም ፋይናንሻል ዶክመንት ኦርጅናል ለብቻ ፋይናንሻል ዶክመንት ኮፒ ለብቻ አሽጎ ለጨረታ በተዘጋጀ ሣጥን ውስጥ በማስገባት መወዳደር የሚችሉ ሲሆን ጨረታው በአርባ ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ግቢ በ16ኛው ቀን ተጫራቾች /ህጋዊ ተወካዮቻቸው) በተገኙበት በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ8፡30 ላይ የሚከፈት ይሆናል፡፡ ሆኖም የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይንም የበዓላት ቀን ላይ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን መዝጊያና መክፈቻ ይሆናል ፡፡
9ኛ. በሌላ ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ ተቀባይነት የለውም ፡፡
10ኛ. መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ::
ለበለጠ መረጃ የስልክ ቁጥር- 0468810369/0468812049 መደወል ይቻላል ፡፡
በደ/ኢ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግሥት በጋሞ ዞን የአ/ም/ከ/ው/አ/ ድርጅት
