በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በ2017 በጀት ዓመት በዞኑ ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች፣ ለወረዳ እና ከተማ አስተዳደር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል የተሸከርካሪ ጎማ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በ2017 በጀት ዓመት በዞኑ ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች፣ ለወረዳ እና ከተማ አስተዳደር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል የተሸከርካሪ ጎማ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
- በዘመኑ የታደሰ የዘርፉ የንግድ ሥራ ፈቃድ ማቅረብ የሚችል፣
- የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፣
- የአቅራቢነት ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፤
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል ያለው፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፤
- ከላይ በዝርዝር የተቀመጠውን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ከጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ግዥና ንብ/አስ/ዋ/ሥራ ሂደት በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ዕቃ የሚያቀርቡት ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆን ይኖርበታል። ቫትን ያላካተተ ከሆነ ቫትን እንዳካተተ ተደርጎ ይቆጠራል፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ፣ ብር 150,000 /አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር/ ሲፒኦ እና ከታወቀ ባንክ በሚሰጥ የክፍያ ማዘዣ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ ወይም በባንክ ዋስትና ሆኖ በጥሬ ገንዘብ ብቻ ዋስትና ማቅረብ አይቻልም፡፡
- ተጫራቾች የሚሸጡበትን ዋጋ በተዘጋጀው ዝርዝር ሰነድ ላይ ዋጋ ሞልተው አንድ ኦርጅናል ሰነድ እና ሁለት ኮፒ ሰነድ በተለያየ ፖስታ ካሸጉ በኋላ ከሲፒአ ጋር በአንድ ትልቅ ፖስታ በሰም በማሸግ ማቅረብ ይገባቸዋል።
- ኦርጅናልና ኮፒ ሰነድ ላይ ማንኛውም አይነት ስርዝ ድልዝ /በፍሉድ/ የተስተካከለ በሚታይ መልኩ በድጋሚ ተጽፎ በተጫራቾች ወይም በህጋዊ ተወካይ መፈረም አለበት።
- በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ ላይ ህጋዊ የድርጅት ማህተምና ፈርማ ማረፍ አለበት።
- ጨረታው የሚከፈተው ይህ ማስታውቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ወጥቶ በአየር ላይ ከዋለበት በተከታታይ በሚቆጠር 15 ቀናት በኋላ በ16ኛው ቀን ጠዋት የጨረታው ሳጥን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ 4:30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ስለሆነም ተጫራቾች በዕለቱ ከጠዋቱ 2:30 እስከ 4፡00 ሠዓት ባለው ጊዜ የመወዳደሪያ ሰነዶቻቸውን በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ 16 ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ጨረታው የሚከፈት ይሆናል፡፡
- የጨረታው ሳጥን የሚገኘው በጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ቅጥር ግቢ ግዥና ንብ/አስ/ዋና ሥራ ሂደት ነው።
- ተጫራቾች በጨረታው ተወዳድረው ያሽነፉበትን ጎማዎች ጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ዕቃ ግምጃ ቤት ድረስ የማጓጓዣ፣ የማስጫኛ እና የማውረጃ ወጪ ችለው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የሚቀርበው የጨረታ ዋጋ ጨረታው ከተከፈተበት ቀን በኋላ ለ3 ወር ማለትም ለ90 ቀናት ጸንቶ ይቆያል።
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር፡- 0461310108 መደወል ይችላሉ፡፡
በጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የግዥና ንብ/አስ/ዋና የሥራ ሂደት
