የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን በ2017 በጀት ዓመት የተለያዩ አይነት የፖሊስ ደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የተለያዩ አይነት ዕቃዎች ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ ማስታወቂያ ቁጥር (ሶስት) 03/2017 ዓ.ም
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን በ2017 በጀት ዓመት የተለያዩ አይነት የፖሊስ ደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች
- ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፤
- የዘመኑ ግብር የተከፈለበት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለው
- የአቅራቢነት ምስክር ወረቀት ያለው
- የታክስ ከፋይነት ምዝገባ የምስክር ወረቀትና ግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ወይም ቲን ሰርተፍኬት ያለው
- የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት ተመዝጋቢ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል
- የትብብር ደ/ቤ ማቅረብ የሚችል
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /Bid Bond/ ለሚያቀርቡት የዕቃ ዋጋ
- የተሞላውን ዋጋ ከብር 50,001.00 እስከ 500,000.00 ከሆነ የብር 5,000.00 በባንክ የተመሠከረለት ቼክ /CPO/ ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የተሞላው ዋጋ ከብር 500,001.00 ከሆነ የብር 1,000,000.00 ከሆነ የብር 10,000.00 በባንክ የተመሰከረለት ቼክ /CPO/ ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የተሞላው ዋጋ ከብር 1,000,001.00 እስከ 5,000,000.00 ከሆነ የብር 50,000.00 በባንክ የተመሰከረለት ቼክ /CPO/ ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የተሞላው ዋጋ ከብር 5,000,001.00 በላይ ከሆነ የብር 100,000.00 በባንክ የተመሰከረለት ቼክ /CPO/ ሌተር ኦፍ ክሬዲት ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች እንድ ተጫራች የሰጠውን ዋጋ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት የተከለከለ ነው የተሞላዉ ዋጋ ከዘጠና ቀናት (90) በታች መሆን የለበትም::
- ተጫራቾች በሰነዶቻቸው ላይ ስማቸውን ሙሉ አድራሻቸውንና ፈርማቸውን አሟልተው ማቅረብ ይኖርባቸዋል
- የቴክኒካል ስፔስፍኬሽን እና የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በቅጂ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቶች ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 50 /ሃምሳ ብር/ በመክፈል ለ15 ተከታታይ ቀናት እስከ ቀኑ 11:00 ሰዓት ድረስ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን ግዥና ፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በመምጣት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረቻ ዋጋቸውን በጨረታ ሰነድ ላይ በተጠቀሰው መሠረት በግልጽ ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታ የሚከፈተው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከ 15ኛው ቀን በኋላ በቀጣዩ የሥራ ቀን ከቀኑ 06:00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው ጨረታውም በዚሁ ዕለት ከሰዓት በኋላ 08:00 ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኮሚሽኑ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል።
- ኮሚሽኑ ከእሸናፊ ተጫራቾች ጋር ውል በሚዋዋልበት ጊዜ 20% የመጨመር ወይንም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው
- ኮሚሽኑ ከአሸናፊ ተጫራቶች ጋር ውል ከተዋዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ ስድስት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ 25% የመጨመር መብት አለው::
- ኮሚሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው::
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች ሞባይል ቁጥር 0910062954 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን
