የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን በ2017 በጀት ዓመት የመደበኛ ፖሊስ ሠራዊት ደንብ ልብስ ሸሚዝና ሱሪ ፣ የፖሊስ ቦቲ ጫማ ፣ የወንድ ጉርድ ጫማ ፣ የሴት ጉርድ ጫማ፣ መለዮ ቲሸርት ካልሲ እና ቀበቶ፣ ሰልጣኝ ምግና አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ የምግብ ሸቀጣሸቀጦች እና አትክልት በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የግዥ ማስታወቂያ ቁጥር (ሁለት) 08/2017 ዓ.ም
የተለያዩ አይነት የፖሊስ ሰራዊት ደንብ ልብስ እና ለሰልጣኝ ምግና አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ሸቀጣሸቀጦች እና አትክልት ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን በ2017 በጀት ዓመት የመደበኛ ፖሊስ ሠራዊት ደንብ ልብስ ሸሚዝና ሱሪ ፣ የፖሊስ ቦቲ ጫማ ፣ የወንድ ጉርድ ጫማ ፣ የሴት ጉርድ ጫማ፣ መለዮ ቲሸርት ካልሲ እና ቀበቶ፣ ሰልጣኝ ምግና አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ የምግብ ሸቀጣሸቀጦች እና አትክልት ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች:-
- ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው
- የዘመኑን ግብር የተከፈለበት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለው
- የአቅራቢነት ምስክር ወረቀት ያለው
- የታክስ ከፋይነት ምዝገባ የምስክር ወረቀትና ግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ወይም ቲን ሰርቲፍኬት ያለው
- የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ተመዝጋቢ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል
- የትብብር ደ/ቤ ማቅረብ የሚችል
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /Bid Bond/ ለሚያቀርቡት የዕቃ ዋጋ የተሞላ ዋጋ ከብር 50,001.00 እስከ 500,000.00 ከሆነ የብር 5,000.00 በባንክ የተመሠከረለት ቼክ/CPO/ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የተሞላው ዋጋ ከብር 500,001.00 እስከ 1,000,000.00 ከሆነ የብር 10,000.00 በባንክ የተመሠከረለት ቼክ /CPO/ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የተሞላው ዋጋ ከብር 1,000,001.00 አስከ 5,000,000.00 ከሆነ የብር 50,000.00 በባንክ የተመሠከረለት ቼክ /CPO/ ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የተሞላ ዋጋ ከብር 5,000,001.00 በላይ ከሆነ የብር 100,000.00 በባንክ የተመሠከረለት ቼክ /CPO/ ሌተር ኦፍ ክሬዲት ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡
- ተጫራቾች እንድ ተጫራች የሰጠውን ዋጋ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት የተከለከለ ነው የተሞላው ዋጋ ከዘጠና ቀናት /90/ በታች መሆን የለበትም፡፡
- ተጫራቾች በሰነዶቻቸው ላይ ስማቸውን ሙሉ አድራሻቸውንና ፊርማቸውን አሟልተው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የቴክኒካል ስፔስፊኬሽን እና የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በቅጂ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች በጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 50 /ሃምሳ ብር/ በመክፈል ለ15 ተከታታይ ቀናት እስከ ቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ግዥናን አስተደደር ዳይሬክቶራት በመምጣት ቢሮ በመምጣት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ዋጋቸውን በጨረታ ሰነድ ላይ በተጠቀሰው መሠረት በግልጽ ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታ የሚከፈተው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከ 5ኛው ቀን በኋላ በቀጣዩ የሥራ ቀን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው ጨረታውም በዚሁ ዕለት ከሰዓት በኋላ 08:00 ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኮሚሽኑ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል።
- ኮሚሽን ከአሽናፊ ተጫራቾች ጋር ውል በሚዋዋልበት ጊዜ 20% የመጨመር ወይንም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነዉ።
- ኮሚሽን ከአሸናፊ ተጫራች ጋር ውል ከተዋዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ ስድስት ወር ጊዜ ውስጥ 25% የመጨመር መብት አለው።
- ኮሚሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች - 0461803097 ወይም በሞባይል ቁጥር ወይም 0912252625
እና 0916861342 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
ወላይታ ሶዶ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን
ወላይታ ሶዶ
