የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ከዚህ በታች በሰንጠረዥ የተገለጸውን ለዲስትሪክታችን ሰራተኞች ለ2017 የበጀት ዓመት አገልግሎት የሚውል ጥቅማጥቅም በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልፅ ጨረታ ጥሪ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ከዚህ በታች በሰንጠረዥ የተገለጸውን ለዲስትሪክታችን ሰራተኞች ለ2017 የበጀት ዓመት አገልግሎት የሚውል ጥቅማጥቅም በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ መለያ ቁጥር:- ኢመአ/ድ/ዳ/መ/ጥ/ድ/ቲ 16/2017 ዓ.ም
- ደንብ ልብስ ፣ ጫማ እና የደህንነት መጠበቂያ
- የደንብ ልብስ ሎት: - 1
- ጫማ ሎት: - 2
- የደህንነት መጠበቂያ ሎት:- 3
ስለሆነም ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ባሉት 15 (አስራ አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት የማይመለስ 400.00 (አራት መቶ) ብር በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000322267979 ገቢ በማድረግ ድሬዳዋ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አካባቢ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና ቢሮ ግዥ ክፍል በመቅረብ የጨረታ ሰነዱን መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ስለሆነም ከታች የተዘረዘሩትን መሥፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው እንዲወዳደሩ ተጋብዘዋል፡፡
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ) ብር በባንክ ሲፒኦ ወይም ዋስትና ማቅረብ ይኖርባቸዋል
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 (አስራ አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት አየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ይዘጋል፡፡ በዚሁ እለትም ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማድረግ ድሬዳዋ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አካባቢ በሚገኘው በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት የመሰብሰቢያ አዳራሽ የሚከፈት መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
ማሳሰቢያ:-
- ዲስትሪክቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- በቅድመ ግምገማ ያለፉ ተጫራቾች ያቀረቡት ናሙና በመ/ቤቱ ናሙና መራጭ ኮሚቴ ታይቶ ተቀባይነት ካገኙት መካከል በዋጋ ዝቅተኛ ሆኖ የተገኘው በአሸናፊነት ይመረጣል፡፡
ለበለጠ መረጃ የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ፡፡
ስልክ ቁጥር 025111-13-13/0927636126/0919008017
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት
