የበቾ ወሊሶ የነበሬዎች ሕብረት ስራ ዩኒየን የተለያየ የፕላስቲክ ፋብሪካ ተረፈ ምርት (ኮረት፤ ሪሳይክል የጥሬ ዕቃ ከረጢት) በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የበቾ ወሊሶ የነበሬዎች ሕብረት ስራ ዩኒየን የተለያየ የፕላስቲክ ፋብሪካ ተረፈ ምርት (ኮረት፤ ሪሳይክል የጥሬ ዕቃ ከረጢት) በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም መግዛት የሚፈልግ ግለሰብ ወይም ድርጅት ከዚህ ቀጥሎ ያሉትን መስፈርቶች በማሟላት ተወዳድሮ መግዛት ይችላል፡፡
ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው፡-
- ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው እና የአመቱን ግብር የከፈሉ እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ለጨረታ ሰነድ ግዢ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በዩኒየኑ የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000087184327 ኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ወይም የኢትዮጵያ ንግድ ባንከ 1000036818348 በመክፈል ሰነዱን ከዩኒየን መውሰድ አለባቸው፡፡
- ለጨረታ ማስረከቢያ ቢድ ቦንድ ማስያዣ ያቀረቡትን ዋጋ 5% በሲፒአ ወይም በባንክ ዋስትና ሰነድ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራች የጨረታ ሰነዶቹን በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ 19/10/2017ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት ዩኒየኑ ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ መክፈቻ ቀን 19/10/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች አንዱ ተጫራች ባቀረበው ዋጋ ላይ ተንተርሰው ዋጋ ማቅረብ የተከለከለ ነው፡፡
- ዩኒየኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- አሸናፊው ተጫራች ያሸነፈውን ንብረት ሙሉ በሙሉ እስከ 10 ቀን ጊዜ ውስጥ ማንሳት ይኖርበታል።
አድራሻ፡- በጅማ መንገድ ከአዲስ አበባ 80ኪ.ሜ ቱሉ ቦሎ ከተማ ላይ እንገኛለን፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- በስልክ ቁጥር 0113420265/0113420140 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን የበቾ ወሊሶ የገበሬዎች ሕብረት ስራ ዩኒየን ኃላፊነቱ የተወሰነ ማህበር
