ብራና ማተሚያ ድርጅት የተለያዩ አይነት ቁርጥራጭ ተረፈ ምርቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 001/2017
ብራና ማተሚያ ድርጅት የተለያዩ አይነት ቁርጥራጭ ተረፈ ምርቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። በዚህም መሠረት በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተገለፁትን መስፈርቶች በማሟላት መሳተፍ ትችላላችሁ።
1ኛ በዘመኑ የታደሰ የንግድ ምዝገባ ማቅረብ የሚችሉ
2ኛ ተጫራቾች ለጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር ሦስት መቶ (300.00) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት (ቅዳሜ እና እሐድን ጨምሮ) ወሎ ሰፈር በሚኘው ዋና መሥሪያ ቤት ቢሮ ቁጥር 32 በአካል በመምጣት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
3ኛ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር 10,000.00 በጥሬ ገንዘብ ወይም በሲፒኦ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
4ኛ ተጫራቾች ያሸፉባቸውን ተረፈ ምርቶች በአምስት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ከፍለው የማንሳት ግዴታ አለባቸው።
5ኛ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከ11ኛው ቀን እስከ 8፡00 ሰዓት (ከሰዓት) ድረስ በሰም በታሸገ ፖስታ ለጨረታ ማስገቢያ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው። ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በእለቱ 8፡00 (ከሰዓት) ታሽጎ 8፡30 (ከሰዓት) በድርጅቱ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል።
6ኛ ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፈል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ከወሎ ሰፈር ወደ ጎተራ በሚወስደው መንገድ 700 ሜትር ላይ በስተግራ በኩል
ብራና ማተሚያ ድርጅት
