Tender Detail

Tender Details

  • Company የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አምቦ ሪጅን
  • Address አምቦ ከተማ ቀበሌ 01 የቤት ቁጥር- የድሮ ሃዮሜ ኮሌጅ ህንፃ ላይ 2ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 14 ፡ ኦሮሚያ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: +251112609777
  • Website
  • Deadline14 Jul 2025, 12:00 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Price600.00
  • opening date2025-07-14 00:00:00
  • Categories Metals And Metal Working , Vehicle tire

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አምቦ ሪጅን የሆኑ ንብረቶች ብረታ ብረቶችን፤ አሮጌ ጎማዎች እና ባዶ በርሜሎችን ባሉበት ሁኔታ እና ቦታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።


 

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

ጨረታ ቁጥር፡-/////ብሔ///-001/2018

 

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪ አገልግሎት አምቦ ሪጅን የሆኑ ንብረቶች ብረታ ብረቶችን፤ አሮጌ ጎማዎች እና ባዶ በርሜሎችን ባሉበት ሁኔታ እና ቦታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

 

.

የዕቃው ዓይነት

ሎት

የሚገኝበት ቦታ

የጨረታ ማስከበሪያ (CPO)

የጨረታው መዝጊያ ቀን

የጨረታው መክፈቻ ቀን

1

ብረቶች (ክሮስአርም፤ ታይ ስትራፕ፤ የድራም ብረቶች)

 

ሎት-1

 

አምቦ ከተማ

 

40,000.00 (አርባ ሺህ ብር ብቻ)

 

ከሐምሌ 07 ቀን 2017 . ከቀኑ 800 ሰዓት

 

ከሐምሌ 07 ቀን 2017 . ከቀኑ 830 ሰዓት

2

አሮጌ ጎማዎች

3

ባዶ በርሜሎች

 

ስለሆነም በጨረታው መካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ነጥቦች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ፡፡

ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በድርጅታችን አካውንት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር (1000254843017 EEU Ambo District Connection Fee) የማይመለስ ብር 600 /ስድስት መቶ ብር/ ገቢ በማድረግ ዘወትር በስራ ስዓት አምቦ ከተማ የዱሮ ሃዮሜ ህንፃ 2 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 14 አምቦ ሪጅን የአቅርቦት ሰንሰለት እና ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ በመምጣት የሚወገዱትን ንብረቶች ዝርዝር መረጃ የያዘ የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡

  1. ተጫራቾች ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነድ ገዝተው ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 300 ሰዓት እስከ 600 ሰዓት፤ ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 700 ሰዓት እስከ 1000 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ንብረቶቹን በሚገኙበት ቦታ በመሄድ መመልከት ይችላሉ፡፡
  2. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን በባንክ በተረጋገጠ (CPO) ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Bid Security) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  3. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን እና የጨረታ ማስከበሪያቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ስማቸውን እና ጨረታ ቁጥር /////ብሔ///-001/2018 በመግለፅ ከላይ በተጠቀሰው ቀን ከቀኑ 800 ሰዓት ድረስ ብቻ በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
  4. ጨረታው ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ተዘግቶ በዛው ቀን ከቀኑ 830 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻው በተገኙበት አምቦ ከተማ የዱሮ ሃዮሜ ኮለጅ ህንፃ 2 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 14 አምቦ ሪጅን የአቅርቦት ሰንሰለት እና ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ በሚገኘው ቢሮ ይከፈታል፡፡
  5. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምሮ መሆን አለበት፡፡
  6. ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 011-2-60-97-77 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
  7. ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

 

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አምቦ ሪጅን

 

Save Tender