ድርጅታችን የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኤጀንሲ ያወጣውን የጥራት መስፈርት የሚያሟሉ እና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ሸቀጦች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት
የኢንዱስትሪ ውጤቶች ግዥ ዳይሬክቶሬት
የሸቀጥ ግዥ ጨረታ (ቁጥር 001/2018)
ድርጅታችን የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኤጀንሲ ያወጣውን የጥራት መስፈርት የሚያሟሉ እና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ሸቀጦች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
1. የበለፀገ አንደኛ ደረጃ የዳቦ ዱቄት 9. ከጥጥ የተመረተ አንሶላ
2. ሩዝ 10. የብርድ ልብስ
3. ፖስታ 11. ፎጣ
4. ማካሮኒ 12. የግድግዳና ቆርቆሮ ሚስማር
5. የልብስ ማጠቢያ ሳሙና 13. የቤት ክዳን ቆርቆሮ
7. የገላ መታጠቢያ ሳሙና 14. የአርማታ ብረት
6. ፈሳሽ የልብስ ማጠቢያ ሳሙና 15. የፕሪንተር ወረቀት
8. ስፖንጅ ፍራሽ እና ትራስ
በጨረታው መካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች:-
- ለሁሉም ምርቶች በጨረታው ላይ መሳተፍ የሚችሉት አምራች ድርጅቶች ብቻ ሲሆኑ በፕሪንተር ወረቀት ጨረታ ለመሳተፍ አምራች፤ አከፋፋይ ወይም አስመጪ መሆን ይችላሉ።
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ የንግድ ምዝገባ ፈቃድ፣ ተጨማሪ ዕሴት ታክስ የተመዘገቡ የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሠርተፍኬት እና የግብር ክሊራንስ ያላቸው መሆን ይገባቸዋል።
- ለጨረታ የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሠነድ የማደመሰስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ቢስ መብራት ከሚገኘው የድርጅቱ ዋና መስርያ ቤት የኢዱስትሪ ውጤቶች ግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ለእያንዳንዱ ምርት በጨረታ ሰነዱ ላይ በተጠቀሰው መሰረት) ለብቻው በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- የጨረታ መወዳደሪያ ዋጋቸውን (financial) እና ከላይ ከተጠቀሱት ህጋዊ ሠነዶች (technical) በተለያየ የታሸገ ኤንቨሎፕ አንድ ኦሪጅናል እንዲሁም አንድ ኮፒ በማድረግ እስከ ሐምሌ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 5:00 ሠዓት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ጨረታው በተመሳሳይ ሐምሌ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 5:10 ሠዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ከጨረታ መዝጊያ ሰዓቱ በኋላ የሚቀርብ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት
የኢንዱስትሪ ውጤቶች ግዥ ዳይሬክቶሬት
ስልክ ቁጥር 0111-28-15-29
www.eiide.com.et.com.et
