በኬሚካል ኢንደስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ለምርት ማሸጊያ የሚውል የአልሚኒየም ሰልፌት ማሸጊያ ፒ.ፒ ከረጢት ብዛት 83,200 ባለ 50 ኪ.ግ የድርጅቱን ሎጎ ያለበት አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ኬኢኮአመኬፋ 001/2025
በኬሚካል ኢንደስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ለምርት ማሸጊያ የሚውል የአልሚኒየም ሰልፌት ማሸጊያ ፒ.ፒ ከረጢት ብዛት 83,200 ባለ 50 ኪ.ግ የድርጅቱን ሎጎ ያለበት አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም
- በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ
- የ2017 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ ፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀትን ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ከጨረታው ሰነድ ጋር የተያያዘውን የዕቃ /ፒ.ፒ ከረጢት ዝርዝር/ እና የከረጢቱን ሳምፕል ሁለት ሁለት የማይመስ ከቴክኒካል አፈሩ ጋር ማቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቾች ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ባሉት የስራ ቀናት አዲስ አበባ ሳሪስ አቦ መርቲ ህንፃ ውስጥ ከአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ቅርንጫፍ ቢሮ የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ/ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋ ከ2% ያላነሰ በሲ.ፒ.ኦ (CPO) ቼክ ወይም በባንኮች የተረጋጋጠ ጋራንቲ ደብዳቤ ከ90 ቀን ያላነሰ በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ቴክኒካል ኦፈርና ፋይናንሺያል አፈር ኦሪጅናልና ኮፒ እያንዳንዳቸው ለየብቻ ታሽገው ቴክኒካል ኦፈር፣ ፋይናንሺያል ኦፈር ተብሎ ተፅፎበት እስከ ነሀሴ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 በፊት ከአዳማ ከተማ 15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው አዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋናው መ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው ነሀሴ 1 ቀን 2017ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰአት ተዘግቶ ቴክኒካል ኦፈሩ ብቻ በዕለቱ ነሀሴ 1 ቀን 2017 ዓ.ም 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋናው መ/ቤት ይከፈታል፡፡
- ፋይናንሽያል ኦፈሩ ነሀሴ 8 ቀን 2017 ዓ.ም 4፡00 ሰአት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋናው መ/ቤት ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ / ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 022 225 0266 / 022 225 0750
ሞባይል 0920935336
በኬሚካል ኢንደስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ
