የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን የተለያዩ የመኪና ጎማዎችን ግዥ በሰነድ ላይ ባለው መስፈረት መሰረት በዘርፉ ላይ ከተሰማሩ አቅራቢዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን የተለያዩ የመኪና ጎማዎችን ግዥ በሰነድ ላይ ባለው መስፈረት መሰረት በዘርፉ ላይ ከተሰማሩ አቅራቢዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቶች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ነጥቦች በማሟላት የጨረታ ሰነድ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
- ተጫራቾች የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21 ተከታታይ ቀናት ብቻ መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች በዚህ የንግድ ዘርፍ የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ ቲን ቫት፤ የንግድ ምዝገባ እና ሰነድ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ የ90 ቀን ዋስትና ያለው ቢድ ቦንድ፣ ቼከ ፣ ሲፒኦ ከጨረታ መክፈቻ ቀን ጀምሮ የሚቆጠር የዋጋውን 5% (አምስት ፐርሰንት) በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ከዶክመንት ጋር አያይዞ ማቅረብ አለበት።
- ጨረታው የሚገባበት እና የሚከፈትበት፡-
- ተጫራቾች የሚገዙበትን ዋጋ በመሙላት በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ በ22ኛው ቀን እስከ 4፡00 ሰዓት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው በዚሁ እለት 4፡00 የሚዘጋ ሲሆን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዚሁ ዕለት በ4፡30 ይከፈታል።
- የጨረታ መከፈቻው ቀን የዕረፍት ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን በተጠቀሰው ሰዓት ተዘግቶ የሚከፈት ይሆናል።
- የመወዳደሪያ መስፈርቶችን ሙሉ ለሙሉ ላሟሉ ተጫራቾች ያቀረቡት ዋጋ ታይቶ አሸናፊው ተጫራች ዝቅተኛ ዋጋ ያቀረበ ይሆናል።
- ከላይ የተዘረዘሩትን መመዘኛዎች በሙሉ አሟልተው የማያቀርቡ ተጫራቾች ከጨረታው የሚሰረዙ መሆኑን እንገልጻለን።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- አዲስ አበባ ጀሞ ሚካኤል አደባባይ ሚካኤል ቤ/ክ ጎን OACF ህንፃ 6ኛ ፎቅ ዋና ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 12 ስልክ፡- 0910645442
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን
