አፋር ጨው ማቀነባበሪያና ማምረቻ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከ2015 ዓ.ም እስከ 2017 በጀት ዓመት ያለውን አጠቃላይ የጥሬ እቃና (ጨው) የምርት እንቅስቃሴ በዝርዝር ወደ ፋብሪካ የገባውን የጨው መጠን ተቀነባብሮ መውጣት ያለበትን የጨው መጠን ከተቀነባበረ በኋላ ወደ ሽያጭ የተላለፈውንና በአመታዊ ቆጠራ ጋር በማስታረቅ የንብረት እንቅስቃሴ ስርአት መርህን በመከተል ምርመራ እንዲሰራ ይፈልጋል፡፡
የኦዲት ጨረታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን አፋር ጨው ማቀነባበሪያና ማምረቻ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በአፋር ክልላዊ መስተዳድር አፍዲራ ወረዳ የጨው ማቀነባበሪያ ከፍቶ እየሰራ ያለ ድርጅት ሲሆን ምርቱን በአዲስ አበባ በሚገኘው ዋናው ቢሮ በኩል በመሸጥ የንግድ ስራ ላይ ተሰማርቶ የሚገኝ ድርጅት ነው፡፡ ከ2015 ዓ.ም እስከ 2017 በጀት ዓመት ያለውን አጠቃላይ የጥሬ እቃና (ጨው) የምርት እንቅስቃሴ በዝርዝር ወደ ፋብሪካ የገባውን የጨው መጠን ተቀነባብሮ መውጣት ያለበትን የጨው መጠን ከተቀነባበረ በኋላ ወደ ሽያጭ የተላለፈውንና በአመታዊ ቆጠራ ጋር በማስታረቅ የንብረት እንቅስቃሴ ስርአት መርህን በመከተል ምርመራ እንዲሰራ ይፈልጋል፡፡ ከዚህ በታች ያሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተወዳዳረዎች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናቶች ውስጥ አስፈላጊው የጨረታ መረጃ በመውሰድ ለስራው የሚፈለገውን ዋጋ እና የማጠናቀቂያ ጊዜ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈለ
- ለስራው በቂ የሰው ኃይል እና የስራ ልምድ ያለው
- የኦዲት ስራውን ተረክቦ በአጭር ጊዜ ማጠናቀቅ እና ማስረከብ የሚችል፡፡
- የ2017 ዓ.ም የኦዲት ፈቃድ ያለው
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር (0911488404) ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን፡፡
አድራሻ፡- ቄራ አካባቢ ከቄራ ወደ ጨርቆስ መሄጃ ኤስ ዲ ህንፃ 7ኛ ፎቅ
