በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ለሰራተኞች የተለያዩ የደንብ አልባሳት፤ ጫማዎች እና የሴፍቲ እቃዎችን በብቃት እና በጥራት ማቅረብ ከሚችሉ ተጫራቾች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ኬኢኮአመኬፋ 003/2025
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ለሰራተኞች የተለያዩ የደንብ አልባሳት፤ ጫማዎች እና የሴፍቲ እቃዎችን በብቃት እና በጥራት ማቅረብ ከሚችሉ ተጫራቾች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም
- በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፤
- የ2017 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀትን ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ለሚያቀርቡት ለእያንዳንዱ አልባሳት ጫማ እና የሴፍቲ እቃዎች አንዳንድ ናሙና ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ባሉት የስራ ቀናት አዲስ አበባ ሳሪስ አቦ መርቲ ህንፃ ውስጥ ከአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ቅርንጫፍ ሽያጭ ቢሮ ወይም ከአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋናው መስሪያ ቤት የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ/ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋ ከ2% ያላነሰ በሲ.ፒ.ኦ (CPO) ቼክ ወይም በባንኮች የተረጋገጠ ጋራንቲ ደብዳቤ ከ90 ቀን ያላነሰ በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ አለባቸው።
- ቴከኒካል ኦፈርና ፋይናንሺያል ኦፈር ኦሪጅናልና ኮፒ እያንዳንዳቸው ለየብቻ ታሽገው ቴክኒካል ኦፈር፣ ፋይናንሺያል ኦፈር ተብሎ ተፅፎበት እስከ ነሀሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 በፊት ከአዳማ ከተማ 15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው አዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋናው መ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው ነሀሴ 26 ቀን 2017ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ ቴክኒካል ኦፈሩ ብቻ በዕለቱ ነሀሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋናው መ/ቤት ይከፈታል፡፡
- ፋይናንሽያል ኦፈሩ የሚከፈትበት ቀን ቴክኒካል ኦፈር በሚከፈትበት ቀን የሚገለጽ ይሆናል፡፡
- ድርጅቱ / ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 022 225 0266/022 225 0750
ሞባይል 0920935336/0911727794
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ
