የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ እና የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በጋራ እየተገለገሉበት የሚገኘው ቢሮ የጽዳት አገልግሎት የሥራ መደቦችን አውትሶርስ አድርጎ ማሰራት በመፈለጉ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ ቁጥር ቤ/ል/ኮ/ግ/ጨ/002/2018 አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ እና የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በጋራ እየተገለገሉበት የሚገኘው ቢሮ የጽዳት አገልግሎት የሥራ መደቦችን አውትሶርስ አድርጎ ማሰራት በመፈለጉ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ ቁጥር ቤ/ል/ኮ/ግ/ጨ/002/2018 አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በዘርፉ የተሰማራችሁ የ2017/2018 ዓ.ም የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ እና የንግድ ምዝገባ ያላችሁ፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፤ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚ/ር የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ በድረ ገፅ ላይ /Online/ የተመዘገቡ እንዲሁም ማስረጃውን ኮፒና ኦርጅናል ማቅረብ የሚችሉ፤ ድርጅቶች ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 01 ባንቢስ አካባቢ ግሪክ ትምህርት ቤት ፊት ለፊት ያለው ህንፃ ላይ 4ተኛ ፎቅ በኮርፖሬሽኑ የፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ቢሮ በመቅረብ የተዘጋጀውን እያንዳንዱን የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚሆን በግልፅ ጨረታ ቁጥር ቤ/ል/ኮ/ግ/ጨ/002/2018 ብር 15,000.00 በባንክ በተረጋገጠ ቼክ (CPO) ወይንም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ከሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ጋር በማያያዝ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ጨረታው የሚከፈተው ነሐሴ 13/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ተወካዮች በተገኙበት በኮርፖሬሽኑ የመንግስት ግዥ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ 9ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 901 ይከፈታል፡፡ ኮርፖሬሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ባንቢስ አካባቢ ግሪክ ት/ቤት ፊት ለፊት በሚገኘው የቤቶች ልማት ህንፃ
ስልክ ቁጥር፡- 0936 99 35 20 / 0949 75 59 34
በቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
