የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለ2018 የአዲስ አመት የመልካም ምኞት መግለጫ ማስታወቂያ በጨረታ መለያ ቁጥር DBE/NCB/BP/06/2024/25 በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ብሔራዊ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለ2018 የአዲስ አመት የመልካም ምኞት መግለጫ ማስታወቂያ በጨረታ መለያ ቁጥር DBE/NCB/BP/06/2024/25 በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
- ተጫራቾች ከጨረታው መልስ ጋር የሚከተሉትን ተጨማሪ ሰነዶችን ያቀርባሉ፡
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ
- የግብር ከፋይ መለያቁጥር /T.I.N/
- የግብር ግዴታ ለመወጣቱ ከሀገር ውስጥ ገቢ ባለሥልጣን ወይም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት የተሰጠ ተጫራቹ የግብር ግዴታ የተወጣ በመሆኑ ጨረታ ላይ መሳተፍ እንደሚችል የሚገልጽ የጽሁፍ ማስረጃ (ጊዜው ያላላፈበት መሆን ይኖርበታል)
- የተ.እ.ታክስ /VAT/ ሰርተፊኬት
- የመንግስት ግዢ እና ንብረት አስተዳደር የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፊኬት
- የማጭበርበር ድርጊት ላለመፈጸም ቃል የሚገባበት ፎርማት ተሞልቶ የተጫራቹ ድርጅት ፊርማና ማህተም የተደረገበት
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 30,000 በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች የዕቃዎቹን ዝርዝር/ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ/ ታወር ሁለት በባንኩ እግረኛ መግቢያ ክፍያውን ፈጽመው ባንኩ በተከራየው ህንጻ ላይ (ኪያሜድ ህንጻ ላይ) 1ኛ ፎቅ ከግዥ ቡድን ቢሮ ሶፍት ኮፒውን መውሰድ ይችላሉ።
- የጨረታ ሰነድ ለተጫራቾች መሸጥ የሚጀምረው ሐምሌ 30 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ነው።
- ተጫራቾች ጥያቄ ካላቸው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ባሉት ተከታታይ አምስት ቀናት ውስጥ ማሳወቅ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ከጨረታ መክፈቻ ሰአት በፊት ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ ጨረታው መጀመሪያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባንኩ በተከራየው ህንጻ ላይ (ኪያሜድ ህንጻ ላይ) ግዥ ክፍል ኦሪጂናል እና ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማሸግ ማስገባት ይችላሉ።
- ጨረታው ነሐሴ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰአት ላይ ታሽጎ ነሐሴ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:05 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ባንኩ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለበለጠ መረጃ 0115-57-80-88 መደወል ይቻላል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
