የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2018 ዓ.ም አገልግሎት ላይ የሚውሉ የተለያዩ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2018 ዓ.ም አገልግሎት ላይ የሚውሉ የተለያዩ ዕቃዎችን ማለትም፡-
1. እላቂ የትምህርት ዕቃዎች
2. አላቂ የጽዳት ዕቃዎች
3. አላቂ የቢሮ ዕቃዎች
4. ቋሚ ዕቃዎች
5. አላቂ የህክምና ዕቃዎች
6. የደንብ ልብሶች እና
7. ልዩ ልዩ መሳሪያዎችን
በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች፡
- ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣
- የተጨማሪ እሴት ታከስ ተመዝጋቢ የሆኑ
- የአቅራቢነት የምስከር ወረቀት ያላቸው
- የጨረታ ማስከበሪያ የጨረታውን 2% CPO ማስያዝ ይኖርባቸዋል
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ /ቫትን ጨምሮ/ በገዙት ሰነድ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ ቦታ በግልጽ በመሙላት ስም፣ ፊርማና ማህተማቸውን ማኖር ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት በት/ቤቱ ፋ/ግ/ን/አስ/ደ/የስ/ሂ ቢሮ ቁ.10 በመግኘት ብር100.00 /አንድ መቶ ብር/ በመከፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ ከሞሉ በኋላ ዋናውንና ኮፒውን በተለያየ ኤንቨሎፕ በማሸግና ማህተም በማድረግ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፤
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለአስር ተከታታይ የስራ ቀናት በአየር ላይ ይቆይና በአስረኛው ቀን በ10፡00 ሰዓት ተዘግቶ ልከ በአስራ አንደኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ጨረታውን አሸናፊ ሆነው ሲገኙ ባሸነፉበት ዋጋ መጠን 10% የውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ ፡- አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከ ወረዳ 07 ክራውን ሆቴል ፌትለፊት
ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ግቢ ውስጥ
አዲስ አበባ ኢትዮጲያ ስልክ፡-0913151293/0911575556/0910567174
በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ት/ት ቢሮ የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት 1ኛና 2ኟ ደረጃ ት/ቤት
