የኢትዮጽያ ፖስታ ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን የግዥ አይነቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡
የቴክኖሎጂ ዕቃዎች ፣ የፖስታ መገልገያዎች የዕቃ መላኪያ ካርቶኖች፣ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃዎች፣ የህትመት ውጤቶች 2018 ዓ.ም በጀት ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 01/2017 ዓ.ም
የኢትዮጽያ ፖስታ ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን የግዥ አይነቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
|
ተ.ቁ |
የጨረታው አይነት |
የሎት አይነት |
የሲፒኦ መጠን |
ጨረታው የወጣበት ቀን |
ጨረታው የሚከፈትበት ጊዜ |
|
1 |
የቴክኖሎጂ እቃዎች |
ሎት 1 |
100,000 |
ነሐሴ 08 ቀን 2017 ዓ.ም |
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም |
|
2 |
የፕሪንተርና የፎቶ ኮፒ ቶነሮች |
ሎት 2 |
100,000 |
||
|
3 |
የመልዕክት መላኪያ ካርቶን |
ሎት 3 |
100,000 |
||
|
4 |
የጽህፈት መሳሪያና የፕሪንተር የፎቶ ኮፒ ቶነሮች |
ሎት 4 |
100,000 |
||
|
5 |
የጽዳት ዕቃዎች |
ሎት 5 |
50,000 |
||
|
6 |
የህትመት ውጤቶች |
ሎት 6 |
100,000 |
በመሆኑም በጨረታው ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች በዘርፋ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ተጫራቾች የማስረጃውን ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችል በድርጅቱ ገንዘብ ቤት 2ኛ ፎቅ የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በየሎቱ በመክፈል ግዥ ክፍል 2ኛ ፎቅ በመቅረብ የጨረታ ሰነድ በመውሰድ ቴክኒካል ፕሮፖዛል እና ፋይናንሻል ፕሮፖዛል ለየብቻ /በተናጠል/ በማድረግ በጨረታ ሠነዱ ላይ በዝርዝር በተገለፀው ሎት መሠረት ዋጋ በመሙላት በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ እስከ ነሐሴ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 6፡30 ድረስ ሠነዱን ከገዙበት ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
በተጨማሪም ተጫራቾች በቅድሚያ ተመላሽ የሚሆን በሁኔታዎች ላይ ያልተመሠረተ የጨረታ ማስከበሪያ በባንከ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO/ በየሎቱ በማሠራት ከኦርጅናል ቴክኒካል ፕሮፖዛል ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታው ኤንቨሎፕ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ነሐሴ 28 ቀን 2017 ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ላይ በድርጅቱ የሠራተኞች ክበብ ይከፈታል፡፡ ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0911954537 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡ /CPO/ ሲያሠሩ ለኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በማለት ያሠሩ
የኢትዮጵያ ፖስታ
