Tender Detail

Tender Details


በሸገር ከተማ በገላን ከፍለ ከተማ የገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በገላን ወረዳ አስተዳደር ስር ላሉ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለ2018 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ፡- የቢሮ የፅህፈት መሳሪያዎችን የቢሮ ፈርኒቸርና ኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን፣ የፅዳትና አላቂ የቢሮ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡


                                                                                 የጨረታ ማስታወቂያ

                                            ገ/ወ/ገ/ጽ/ቤት ጨረታ ቁጥር 001/2018

በሸገር ከተማ በገላን ከፍለ ከተማ የገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በገላን ወረዳ አስተዳደር ስር ላሉ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለ2018 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ፡- የቢሮ የፅህፈት መሳሪያዎችን የቢሮ ፈርኒቸርና ኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን፣ የፅዳትና አላቂ የቢሮ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ 

ስለሆነም በጨረታው ስመሳተፍ- 

  1. በዘርፉ ህጋዊ እና የታደሰ የንግድ ፍቃድ እና የግብር መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ፡፡ 

  2. በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዘጋቢ የሆኑ እና ማቅረብ የሚችሉ፡፡  

  3. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት እለት አንስቶ ለ15/ለአስራ አምስት/ የሰራ ቀናት ለእያንዳንዳቸው የጨረታ ሰነድ በማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር /በገላን ወረዳ ገቢዎች ጽ/ ቤት ሲንቄ ባንከ ቁጥር 1064793701213 በመክፈል የጨረታውን ሰነድ ከገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት መውሰድ ይችላሉ፡፡ 

  4. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋጋ በመሙላት ኦርጅናል እና ኮፒ ለየብቻ በፖስታ በማሸግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው/አስራ ስድስተኛው የስራ ቀናት በገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ከረፋዱ እስከ 4፡00 ሰዓት ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ 

  5. ጨረታው በአስራ ስድስተኛው የስራ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ እለት ከረፋዱ 4፡30 በገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ሆኖም ጨረታው በሚከፈትበት ሰዓት ተጫራቾች ባይገኙም _ ጨረታውን _ ከመከፈት አያግደውም፡፡ 

  6. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚውል በባንክ በተረጋገጠ Cpo/ሲፒኦ/ ለቢሮ ጽሕፈት መሳሪያዎች 30,000/ሰላሳ ሺህ/ ለቢሮ ቋሚ ፈርኒቸር እና ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች 50,000/ሀምሳ ሺህ/ ለቢሮ ፅዳት እና አላቂ እቃዎች 20,000/ሃያ ሺህ /ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ 

  7. ተጫራቾች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡ 

  8. ተጫራቾች በጨረታው ሰነድ ዝርዝር መሰረት ሞልተው መመለስ ይኖርባቸዋል፡፡ 

  9. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡  ለተጨማሪ መረጃ፦ 0913321839/0910742350

                                                                 በገላን ክፍለ ከተማ የገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት 

Save Tender