Tender Detail

Tender Details


የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት በ2018 በጀት ከዚህ በታች የተዘረዘሩ የሽያጭና የአገልግሎት ግዥ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛትና ለመሸጥ ይፈልጋል።


 

የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር 001/ሽያጭና አገልግሎት/18 .

 

የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት 2018 በጀት ከዚህ በታች የተዘረዘሩ የሽያጭና የአገልግሎት ግዥ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛትና ለመሸጥ ይፈልጋል፡-

1 ለምግብነት የሚውል ንፁህ ስንዴ፣ ጤፍ፣ ገብስ፣ ቦሎቄ እና የእህል ሰብል ብጣሪዎች ሽያጭ

2 2017/2018 / የሂሳብ ኦዲት አገልግሎት ጨረታ

3 የትራንስፖርት ማጓጓዣ አገልግሎት ጨረታ

4 ያገለገለ መኪና፣ የእርሻ ትራክተር ከነማረሻው የተለያዩ ያገለገሉ ዕቃዎች ሽያጭ ጨረታ

በዚሁ መሠረት:

  • ተጫራቾች በሥራ ዘርፉና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች ህጋዊ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸውና የዘመኑን የመንግሥት ግብር አጠናቀው ስለመፈላቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
  • ተጫራቾች ለጨረታው ውድድር ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ የጨረታ ማስረከቢያ በባንክ የተመሰከረለት የክፍያ ማዘዣ (CPO) በጨረታ ሰነድ ላይ የሚገለጽ ይሆናል፡፡
  • የጨረታው ሰነድ ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን ድረስ የማይመለስ ብር 400.00 በመፈል በሀዋሳ ከተማ በድርጅቱ የግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 መግዛት ይችላሉ፡፡
  • ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 የስራ ቀናት ውስጥ በሰም በታሸገ ፖስታ /ኤንቨሎፕ/ በማድረግ ኦሪጂናልና ኮፒውን ለየብቻው ከተጓዳኝ ማስረጃዎች ጋር በማደራጀት በድርጅቱ የግዥ ፋይ//አስ/ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ 15ኛው ቀን እስከ 800 ሰዓት ማስገባት አለባቸው
  • የጨረታው ሳጥን የጨረታው ማስታወቂያ በወጣ 15 ኛው ቀን ከቀኑ 800 ሰዓት ታሽጐ በእለቱ 830 ሰዓት በድርጅቱ ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው/በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ነገር ግን 15ኛው ቀን የሥራ ቀን ባይሆን በቀጣዩ የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ተመሳሳይ ቦታ ሰዓትና ሁኔታ ይከፈታል፡፡
  • ድርጅቱ ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  • ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎች በሚዘጋጀው የጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይቻላል
  • ስልክ ቁጥር 046 220 1752/2285/2117

 

የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት

Save Tender